-
ከግብፅ ሃብት የሚልቅ ነገርመጠበቂያ ግንብ—2002 | ሰኔ 15
-
-
ሙሴ ወደ ፈርዖን ልጅ ከተመለሰ በኋላ “የግብፆችን ጥበብ ሁሉ” ተማረ። (ሥራ 7:22) ይህ ለመንግሥት ባለ ሥልጣንነት የሚያበቃ ሥልጠና ማግኘትንም ይጨምራል። የግብጻውያን ትምህርት ሒሳብን፣ ጂኦሜትሪን፣ የሕንጻ ጥበብን፣ ግንባታን እንዲሁም የተለያዩ የሥነ ጥበብ ዘርፎችንና ሳይንስን ያካትታል። ምናልባትም ንጉሣዊው ቤተሰብ ሙሴ የግብጽን ሃይማኖት እንዲማር ማድረግ ፈልጎም ይሆናል።
ሙሴ ይህንን ከፍተኛ ትምህርት የወሰደው ከሌሎች የንጉሣውያን ቤተሰብ ልጆች ጋር መሆን አለበት። እንዲህ ዓይነቱን ከፍተኛ ትምህርት የመማር መብት ካገኙት መካከል “‘ከሰለጠኑ’ በኋላ ወደ አገራቸው ተመልሰው” የፈርዖን ታማኝ “ሎሌዎች በመሆን እንዲያገለግሉ ወደ ግብጽ የተላኩ ወይም በምርኮኛነት የመጡ የውጪ አገር ገዢዎች ልጆች” ይገኙበታል። (በቤትሲ ኤም ብራያን የተዘጋጀው የቱትሞስ አራተኛ የግዛት ዘመን የተባለው መጽሐፍ) በንጉሣዊው ቤተ መንግሥት ሥር ባሉት የሕፃናት ማሳደጊያዎች ውስጥ የሚያድጉት ወጣቶች የቤተ መንግሥት ባለሟሎች ሆነው ለማገልገል የሚያስችላቸውን ሥልጠና ያገኙ የነበረ ይመስላል።a መካከለኛና አዲስ በመባል በሚታወቁት የግብጽ ሥርወ መንግሥታት ዘመን በድንጋይ ላይ የተቀረጹ ጽሑፎች እንደሚያሳዩት ከፈርዖን የቅርብ ባለሟሎችና ከፍተኛ ባለ ሥልጣናት መካከል አብዛኞቹ ትልልቅ ሰዎች ከሆኑም በኋላ እንኳ ሳይቀር “የሕፃናት ማሳደጊያው ልጆች” በሚል የማዕረግ ስም ይጠሩ ነበር።
-
-
ከግብፅ ሃብት የሚልቅ ነገርመጠበቂያ ግንብ—2002 | ሰኔ 15
-
-
a ይህ ትምህርት ዳንኤልና ጓደኞቹ በባቢሎን የመንግሥት ባለሥልጣናት ከመሆናቸው በፊት ከተሰጣቸው ትምህርት ጋር የሚመሳሰል ሊሆን ይችላል። (ዳንኤል 1:3-7) የዳንኤልን ትንቢት በትኩረት ተከታተል! በሚል ርዕስ በይሖዋ ምሥክሮች የተዘጋጀውን መጽሐፍ ምዕራፍ 3 ተመልከት።
-