የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • “ስለ ኢየሱስ የሚገልጸውን ምሥራች” ማወጅ
    ‘ስለ አምላክ መንግሥት በሚገባ መመሥከር’
    • 3. (ሀ) ፊልጶስ ማን ነው? (ለ) የስብከቱ ሥራ በሰማርያ እምብዛም ያልተስፋፋው ለምን ነበር? ይሁንና ኢየሱስ በዚያ አካባቢ ምን እንደሚሆን አስቀድሞ ተናግሯል?

      3 ‘ከተበተኑት ደቀ መዛሙርት’ አንዱ ፊልጶስ ነው።a (ሥራ 8:4፤ “‘ወንጌላዊው’ ፊልጶስ” የሚለውን ሣጥን ተመልከት።) ፊልጶስ የሄደው ወደ ሰማርያ ነው፤ የሰማርያ ከተማ ከስብከቱ ሥራ አንጻር በአብዛኛው ያልተነካ ክልል ነበር። ምክንያቱም በአንድ ወቅት ኢየሱስ ለሐዋርያቱ “ወደ ማንኛውም የሳምራውያን [ከተማ] አትግቡ፤ ከዚህ ይልቅ ከእስራኤል ቤት ወደጠፉት በጎች ብቻ ሂዱ” የሚል መመሪያ ሰጥቷቸው ነበር። (ማቴ. 10:5, 6) ሆኖም ኢየሱስ ከጊዜ በኋላ በሰማርያ ምሥራቹ በሚገባ እንደሚሰበክ ያውቅ ነበር፤ ወደ ሰማይ ከማረጉ በፊት “በኢየሩሳሌም፣ በመላው ይሁዳና በሰማርያ እንዲሁም እስከ ምድር ዳር ድረስ ምሥክሮቼ ትሆናላችሁ” ያለው ለዚህ ነው።—ሥራ 1:8

  • “ስለ ኢየሱስ የሚገልጸውን ምሥራች” ማወጅ
    ‘ስለ አምላክ መንግሥት በሚገባ መመሥከር’
    • a ይሄኛው ፊልጶስ ሐዋርያው ፊልጶስ አይደለም። ከዚህ ይልቅ በዚህ መጽሐፍ ምዕራፍ 5 ላይ እንደተመለከትነው ‘መልካም ስም ያተረፉ ሰባት ወንዶች’ ከተባሉት አንዱ ነው፤ እነዚህ ወንድሞች በኢየሩሳሌም ለሚኖሩት ግሪክኛ ተናጋሪና ዕብራይስጥ ተናጋሪ መበለቶች በየዕለቱ ምግብ የማከፋፈሉን ሥራ እንዲያስተባብሩ የተሾሙ ናቸው።—ሥራ 6:1-6

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ