-
ሶርያ—የጥንታዊ ታሪክ አሻራንቁ!—2003 | ሚያዝያ 8
-
-
በዘመናዊቷ ደማስቆ አብርሃም በዚያ ማለፉን ወይም ዳዊት ወርሯት እንደነበረ የሚያሳይ ማስረጃ አናገኝም። ይሁን እንጂ የጥንቱ የሮማውያን ከተማና በጥንት ሮማውያን ዘመን ቪያ ሬክታ የሚባለውና በአሮጌው ከተማ ያልፍ የነበረው ዋነኛ ጎዳና (ቅን የተባለ ጎዳና) ቅሬታዎች አሁንም አሉ። ሳውል ከደማስቆ ወጣ ብሎ ተአምራዊ በሆነ መንገድ ወደ ክርስትና ከተለወጠ በኋላ ከሐናንያ ጋር የተገናኘው በዚህ ጎዳና ላይ በሚገኝ ቤት ውስጥ ነበር። (ሥራ 9:10-19) ዛሬ ያለው ጎዳና በሮማውያን ዘመን ከነበረው ፈጽሞ የተለየ ቢሆንም ሐዋርያው ጳውሎስ የሰባኪነት ሥራውን የጀመረው በዚሁ ቦታ ነበር። ቅን ጎዳና የሚያልቀው በሮማውያኑ የባብ ሻርቂ በር ነው። የከተማይቱ ቅጥሮች ከአናታቸው ቤት የተሠራባቸው እንደነበሩ መገንዘባችን ጳውሎስ በቅርጫት ተደርጎ ከቅጥሩ እንዲወርድና እንዲያመልጥ የተደረገበትን ሁኔታ እንድንረዳ ያስችለናል።—ሥራ 9:23-25፤ 2 ቆሮንቶስ 11:32, 33
-
-
ሶርያ—የጥንታዊ ታሪክ አሻራንቁ!—2003 | ሚያዝያ 8
-
-
በዘመናዊቷ ደማስቆ አብርሃም በዚያ ማለፉን ወይም ዳዊት ወርሯት እንደነበረ የሚያሳይ ማስረጃ አናገኝም። ይሁን እንጂ የጥንቱ የሮማውያን ከተማና በጥንት ሮማውያን ዘመን ቪያ ሬክታ የሚባለውና በአሮጌው ከተማ ያልፍ የነበረው ዋነኛ ጎዳና (ቅን የተባለ ጎዳና) ቅሬታዎች አሁንም አሉ። ሳውል ከደማስቆ ወጣ ብሎ ተአምራዊ በሆነ መንገድ ወደ ክርስትና ከተለወጠ በኋላ ከሐናንያ ጋር የተገናኘው በዚህ ጎዳና ላይ በሚገኝ ቤት ውስጥ ነበር። (ሥራ 9:10-19) ዛሬ ያለው ጎዳና በሮማውያን ዘመን ከነበረው ፈጽሞ የተለየ ቢሆንም ሐዋርያው ጳውሎስ የሰባኪነት ሥራውን የጀመረው በዚሁ ቦታ ነበር። ቅን ጎዳና የሚያልቀው በሮማውያኑ የባብ ሻርቂ በር ነው። የከተማይቱ ቅጥሮች ከአናታቸው ቤት የተሠራባቸው እንደነበሩ መገንዘባችን ጳውሎስ በቅርጫት ተደርጎ ከቅጥሩ እንዲወርድና እንዲያመልጥ የተደረገበትን ሁኔታ እንድንረዳ ያስችለናል።—ሥራ 9:23-25፤ 2 ቆሮንቶስ 11:32, 33
-