-
“የይሖዋ ቃል . . . እየተስፋፋ ሄደ”‘ስለ አምላክ መንግሥት በሚገባ መመሥከር’
-
-
በሐዋርያት ሥራ 12:1-25 ላይ የተመሠረተ
1-4. ጴጥሮስ ምን አስቸጋሪ ሁኔታ አጋጠመው? አንተ በእሱ ቦታ ብትሆን ኖሮ ምን ይሰማህ ነበር?
ግዙፍ የሆኑት የብረት በሮች ከጴጥሮስ ኋላ ጓ ብለው ተዘጉ። ጴጥሮስ ከሁለት ወታደሮች ጋር በሰንሰለት እንደተቆራኘ ወደሚታሰርበት ክፍል ተወሰደ። መጨረሻው ምን ይሆን? ጴጥሮስ የሚያውቀው ነገር አልነበረም፤ ፍርዱን የሚሰማው ከብዙ ሰዓታት ምናልባትም ከቀናት የእስር ቤት ቆይታ በኋላ ነው። ወዲያ ወዲህ ቢያማትር ዓይኑ የሚያርፍበት ነገር የለም፤ የታሰረበት ክፍል ግድግዳና በር ዙሪያውን ከብቦታል፤ ከእጁ ሰንሰለትና ከሚጠብቁት ወታደሮች በቀር ምንም የሚታይ ነገር የለም።
2 በመጨረሻም ጴጥሮስ ከባድ ቅጣት እንደተወሰነበት ሰማ። ንጉሥ ሄሮድስ አግሪጳ ቀዳማዊ፣ ጴጥሮስን ለማስገደል ቆርጦ ተነስቷል።a እንዲያውም ከፋሲካ በዓል በኋላ ይህን ለማድረግ አስቧል፤ በጴጥሮስ ላይ የሞት ብይን በማስተላለፍ ሕዝቡን ማስደሰት ፈልጓል። ይህ እንዲያው ተራ ዛቻ አልነበረም። ከጴጥሮስ ጋር ከሚያገለግሉት ሐዋርያት አንዱ የሆነው ያዕቆብ በቅርቡ በዚሁ ገዢ ተገድሏል።
-
-
“የይሖዋ ቃል . . . እየተስፋፋ ሄደ”‘ስለ አምላክ መንግሥት በሚገባ መመሥከር’
-
-
7, 8. ጴጥሮስ በታሰረበት ጊዜ ጉባኤው ምን አደረገ?
7 አግሪጳ እንዳሰበውም የያዕቆብ መገደል አይሁዳውያኑን አስደሰታቸው። ይህን ሲያይ የልብ ልብ ስለተሰማው ጴጥሮስንም ለመግደል ተነሳሳ። በመሆኑም በዚህ ምዕራፍ መግቢያ ላይ እንደተጠቀሰው ጴጥሮስን እስር ቤት አስገባው። ይሁንና በዚህ መጽሐፍ ምዕራፍ 5 ላይ እንደተጠቀሰው እስር ቤትም እንኳ ሐዋርያቱን ሊገታቸው የማይችልበት ጊዜ አለ፤ አግሪጳ ይህን ሳያስታውስ አይቀርም። ጴጥሮስ ምንም ዓይነት ማምለጫ ቀዳዳ እንዳያገኝ በማሰብ ከ2 ጠባቂዎች ጋር በሰንሰለት እንዲቆራኝ አደረገ፤ እንዲሁም 16 ጠባቂዎች ቀንና ሌሊት እየተፈራረቁ እንዲጠብቁት መደበ። ጴጥሮስ ካመለጠ ጠባቂዎቹ ለእሱ የታሰበውን ቅጣት ይቀበላሉ። እንዲህ ባለው አስጨናቂ ሁኔታ ውስጥ የጴጥሮስ የእምነት ባልንጀሮች ምን ያደርጉ ይሆን?
-