-
“በደስታና በመንፈስ ቅዱስ ተሞሉ”‘ስለ አምላክ መንግሥት በሚገባ መመሥከር’
-
-
5. በርናባስና ሳኦል በቆጵሮስ ደሴት የሰበኩት እንዴት ነው?
5 በርናባስና ሳኦል በአንጾኪያ አቅራቢያ ወደምትገኘው ወደ ሴሌውቅያ ወደብ በእግራቸው ተጓዙ፤ ከዚያም መርከብ ተሳፍረው 200 ኪሎ ሜትር ርቃ ወደምትገኘው የቆጵሮስ ደሴት አቀኑ።d በርናባስ የቆጵሮስ ተወላጅ እንደመሆኑ መጠን ለአገሩ ሰዎች ምሥራቹን ለመንገር ጓጉቶ እንደሚሆን ጥርጥር የለውም። በመጨረሻም በደሴቲቱ ምሥራቃዊ ጠረፍ ወደምትገኘው ስልማና ከተማ ደረሱ፤ ጊዜ ሳያጠፉም “የአምላክን ቃል በአይሁዳውያን ምኩራቦች ማወጅ ጀመሩ።”e (ሥራ 13:5) ከዚህኛው የቆጵሮስ ጫፍ ተነስተው ደግሞ እስከ ሌላኛው ጫፍ ድረስ ተጓዙ፤ እግረ መንገዳቸውን ደሴቲቱ ላይ ባሉ ዋና ዋና ከተሞች ውስጥ ምሥራቹን ሰብከው መሆን አለበት። እነዚህ ሚስዮናውያን የትኛውን መንገድ ይዘው እንደተጓዙ ባናውቅም በጥቅሉ 160 ኪሎ ሜትር ገደማ ሳይጓዙ አልቀሩም!
-
-
“በደስታና በመንፈስ ቅዱስ ተሞሉ”‘ስለ አምላክ መንግሥት በሚገባ መመሥከር’
-
-
d በመጀመሪያው መቶ ዘመን፣ አንድ መርከብ የነፋሱ ሁኔታ ጥሩ ከሆነ በቀን 160 ኪሎ ሜትር ገደማ ይጓዝ ነበር። የአየሩ ሁኔታ አመቺ በማይሆንበት ጊዜ ደግሞ ጉዞው ረዘም ያለ ጊዜ ሊወስድ ይችላል።
-