-
“ከይሖዋ ባገኙት ሥልጣን በድፍረት” ተናገሩ‘ስለ አምላክ መንግሥት በሚገባ መመሥከር’
-
-
8. ጳውሎስና በርናባስ ኢቆንዮንን ለቅቀው የሄዱት ለምንድን ነው? እነሱ ከተዉት ምሳሌስ ምን እንማራለን?
8 ከተወሰነ ጊዜ በኋላ በኢቆንዮን ያሉት ተቃዋሚዎች ጳውሎስንና በርናባስን ለመውገር ሴራ ጠነሰሱ። እነዚህ ሁለት ሚስዮናውያን ይህን ሲሰሙ ወደ ሌላ የአገልግሎት ክልል ለመሄድ ወሰኑ። (ሥራ 14:5-7) በዛሬው ጊዜ ያሉ የመንግሥቱ አዋጅ ነጋሪዎችም ተመሳሳይ የሆነ የጥበብ እርምጃ ይወስዳሉ። ሰዎች የቃላት ጥቃት ሲሰነዝሩብን በድፍረት ምላሽ እንሰጣለን። (ፊልጵ. 1:7፤ 1 ጴጥ. 3:13-15) የኃይል ጥቃት የመሰንዘር አዝማሚያ እንዳለ ካስተዋልን ግን የራሳችንንም ሆነ የእምነት ባልንጀሮቻችንን ሕይወት አደጋ ላይ የሚጥል ነገር አናደርግም።—ምሳሌ 22:3
-