የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • “ከይሖዋ ባገኙት ሥልጣን በድፍረት” ተናገሩ
    ‘ስለ አምላክ መንግሥት በሚገባ መመሥከር’
    • 8. ጳውሎስና በርናባስ ኢቆንዮንን ለቅቀው የሄዱት ለምንድን ነው? እነሱ ከተዉት ምሳሌስ ምን እንማራለን?

      8 ከተወሰነ ጊዜ በኋላ በኢቆንዮን ያሉት ተቃዋሚዎች ጳውሎስንና በርናባስን ለመውገር ሴራ ጠነሰሱ። እነዚህ ሁለት ሚስዮናውያን ይህን ሲሰሙ ወደ ሌላ የአገልግሎት ክልል ለመሄድ ወሰኑ። (ሥራ 14:5-7) በዛሬው ጊዜ ያሉ የመንግሥቱ አዋጅ ነጋሪዎችም ተመሳሳይ የሆነ የጥበብ እርምጃ ይወስዳሉ። ሰዎች የቃላት ጥቃት ሲሰነዝሩብን በድፍረት ምላሽ እንሰጣለን። (ፊልጵ. 1:7፤ 1 ጴጥ. 3:13-15) የኃይል ጥቃት የመሰንዘር አዝማሚያ እንዳለ ካስተዋልን ግን የራሳችንንም ሆነ የእምነት ባልንጀሮቻችንን ሕይወት አደጋ ላይ የሚጥል ነገር አናደርግም።—ምሳሌ 22:3

  • “ከይሖዋ ባገኙት ሥልጣን በድፍረት” ተናገሩ
    ‘ስለ አምላክ መንግሥት በሚገባ መመሥከር’
    • ኢቆንዮን በገላትያ ክልል ያሉት ሊቃኦንያ እና ፍርግያ በሚዋሰኑበት ቦታ ላይ ትገኝ ነበር። ሲሴሮን እና ስትራቦን ጨምሮ አንዳንድ የጥንት ታሪክ ጸሐፊዎች ኢቆንዮን የሊቃኦንያ ከተማ እንደሆነች ገልጸዋል፤ ደግሞም ከመልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ አንጻር ስትታይ ከተማዋ የምትገኘው በዚህ ክልል ውስጥ ነበር። ይሁን እንጂ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ፣ ኢቆንዮንን ‘የሊቃኦንያ ቋንቋ’ ከሚነገርባቸው የሊቃኦንያ ከተሞች ለይቶ ይጠቅሳታል። (ሥራ 14:1-6, 11) በዚህ የተነሳ ተቺዎች የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ትክክል አይደለም በማለት ይከራከሩ ነበር። ሆኖም በ1910 የአርኪኦሎጂ ባለሙያዎች በከተማዋ ውስጥ የተቀረጹ ጽሑፎች አገኙ፤ እነዚህ ጽሑፎች ጳውሎስና በርናባስ ኢቆንዮን ከሄዱ በኋላ ባሉት ሁለት መቶ ዓመታት በከተማዋ የሚነገረው የፍርግያ ቋንቋ እንደነበር ይጠቁማሉ። በመሆኑም የሐዋርያት ሥራ ጸሐፊ ኢቆንዮንን ከሊቃኦንያ ከተሞች ለይቶ መጥቀሱ ትክክል ነው።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ