-
‘ልባችንን ይሞላዋል’መጠበቂያ ግንብ—2013 | ሐምሌ 1
-
-
ይሖዋ በእርግጥ ስለ እኛ ያስባል? ወይስ በምድር ላይ ያሉት ሰዎች ለሚደርስባቸው ሥቃይና መከራ ደንታ የለውም? መጽሐፍ ቅዱስ ለዚህ ጥያቄ የሚሰጠው መልስ የሚያጽናና ነው። አምላክ ለሰው ልጆች እንደሚያስብ እና ደስተኛ ሕይወት እንድንመራ እንደሚፈልግ እርግጠኞች መሆን እንችላለን። አምላክ ለሰው ልጆች በሙሉ ሌላው ቀርቶ እሱን ለማያመሰግኑት ሰዎች እንኳ በየቀኑ ብዙ ጥሩ ነገሮችን ይሰጣቸዋል። ሐዋርያው ጳውሎስ ምን እንዳለ ተመልከት።—የሐዋርያት ሥራ 14:16, 17ን አንብብ።
ጳውሎስ የይሖዋ አምላኪዎች ላልነበሩት የልስጥራ ከተማ ነዋሪዎች እንዲህ ብሏቸዋል፦ “[አምላክ] ባለፉት ትውልዶች ሕዝቦች ሁሉ በራሳቸው መንገድ እንዲሄዱ ፈቀደላቸው፤ ይሁንና መልካም ነገሮች በማድረግ ለራሱ ምሥክር ከማቅረብ ወደኋላ አላለም፤ ከሰማይ ዝናብ በማዝነብ እንዲሁም ፍሬያማ ወቅቶችን በመስጠት የተትረፈረፈ ምግብ ያቀርብላችኋል፣ ልባችሁንም በደስታ ይሞላዋል።” እነዚህ ቃላት ለጳውሎስ አድማጮች ምን ትርጉም ነበራቸው?
-
-
‘ልባችንን ይሞላዋል’መጠበቂያ ግንብ—2013 | ሐምሌ 1
-
-
ይሖዋ የመምረጥ ነፃነት ሰጥቶናል። ይሖዋ ሁሉም ሕዝቦች “በራሳቸው መንገድ እንዲሄዱ” እንደፈቀደላቸው ልብ በል። ለመጽሐፍ ቅዱስ ተርጓሚዎች የተዘጋጀ አንድ የማመሳከሪያ ጽሑፍ እንደሚናገረው፣ ይህ ሐረግ “ደስ ባላቸው መንገድ እንዲሄዱ” ወይም “የተሻለ ነው ብለው ያሰቡትን እንዲያደርጉ” አምላክ እንደፈቀደላቸው የሚያሳይ ሊሆን ይችላል። ይሖዋ፣ አምልኮ እንዲያቀርብለት ማንንም ሰው አያስገድድም። የመምረጥ ነፃነት ሰጥቶናል፤ በመሆኑም ሕይወታችንን የምንመራበትን አቅጣጫ መምረጥ እንችላለን።—ዘዳግም 30:19
-