-
በደም ሕይወትን ማዳን—እንዴት?መጠበቂያ ግንብ—1991 | ሰኔ 15
-
-
7, 8. አምላክ ስለ ደም ያወጣው ሕግ ለክርስቲያኖች እንደሚሠራ ግልጽ የሆነው እንዴት ነው?
7 ከጊዜ በኋላ የክርስቲያን የአስተዳደር አካል ስብሰባ አድርጎ ክርስቲያኖች ሁሉንም የእስራኤል ሕጎች መጠበቅ እንዳለባቸውና እንደሌለባቸው ሲወስን ምን እንደተፈጸመ ታሪክ ያሳየናል። እነርሱም በመለኮታዊ ኃይል እየተመሩ ክርስቲያኖች የሙሴን ሕግ ለመጠበቅ እንደማይገደዱ ነገር ግን “ለጣዖት ከተሠዋ፣ ከደምም፣ ከታነቀም (ደሙ ካልፈሰሰ ሥጋ)፣ ከዝሙትም” መራቃቸው ‘አስፈላጊ’ እንደሆነ ተናገሩ። (ሥራ 15:22-29) በዚህም መንገድ ከደም መራቁ ከዝሙትና ከከባድ የሥነ ምግባር ኃጢአት የመራቅን ያህል አስፈላጊ መሆኑን ግልጽ አደረጉ።a
8 የጥንቶቹ ክርስቲያኖች መለኮታዊውን ዕገዳ ያከብሩ ነበር። እንግሊዛዊው ምሁር ጆሴፍ ቤንሰን በዚህ ላይ አስተያየታቸውን ሲሰጡ እንዲህ አሉ፦ “ይህ ለኖኅና ለወደፊት ዝርያዎቹ የተሰጠውና ለእስራኤላውያን የተደገመው ደምን በመብላት ላይ የተደረገ ዕገዳ . . . በፍጹም አልተሰረዘም። እንዲያውም በተቃራኒው በአዲስ ኪዳን ውስጥ በሥራ ምዕራፍ 15 ላይ ይበልጥ ተረጋግጧል። በዚህም መንገድ የዘላለም ግዴታ ሆኗል።” ይሁንና መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ደም የሚናገረው ነገር በኖኅ ዘመን ወይም በሐዋርያት ዘመን ጥቅም ላይ ያልዋሉትን ደምን ከሰው ወደ ሰው እንደማዘዋወር ያሉ ዘመናዊ የሕክምና ዘዴዎችን ይከለክላልን?
-