-
በተሰሎንቄ ለምሥራቹ መታገልመጠበቂያ ግንብ—2012 | ሰኔ 1
-
-
እነዚህ ሰዎች “ጳውሎስና ሲላስንም አምጥተው ለረብሻ የተሰበሰበው ሕዝብ ፊት ለማቅረብ የያሶንን [ጳውሎስን በእንግድነት የተቀበለውን ሰው] ቤት ሰብረው ገቡ።” ይሁንና ጳውሎስን እዚያ አላገኙትም። በመሆኑም “ያሶንንና አንዳንድ ወንድሞችን እየጎተቱ ወስደው የከተማዋ ገዥዎች ፊት በማቅረብ እንዲህ እያሉ ጮኹ፦ ‘ዓለምን ሁሉ ያናወጡት እነዚያ ሰዎች እዚህም አሉ።’”—የሐዋርያት ሥራ 17:5, 6
ተሰሎንቄ የመቄዶንያ ዋና ከተማ በመሆኗ የራስ ገዝ አስተዳደር ነበራት። ይህ መስተዳድር ደግሞ በከተማዋ ውስጥ ለሚነሱ ችግሮች እልባት የሚሰጥ የሕዝብ ምክር ቤት ነበረው። “የከተማዋ ገዥዎች” ወይም “ፓለታርክ”b የተባሉት ሰዎች ሥርዓት የማስከበር እንዲሁም ሮም ጣልቃ እንድትገባና ከተማዋ ያላትን መብቶች እንድታጣ የሚያደርጉ ሁኔታዎችን የመከላከል ኃላፊነት ያለባቸው ከፍተኛ ባለሥልጣናት ናቸው። በመሆኑም እነዚህ ባለሥልጣናት፣ “ሁከት ፈጣሪዎች” የከተማዋን ሰላም እያደፈረሱት እንዳለ የሚገልጸውን ክስ ሲሰሙ እንደሚደናገጡ የታወቀ ነው።
-
-
በተሰሎንቄ ለምሥራቹ መታገልመጠበቂያ ግንብ—2012 | ሰኔ 1
-
-
b ይህ ቃል በግሪክ የሥነ ጽሑፍ ሥራዎች ውስጥ አይገኝም። ይሁንና በተሰሎንቄ አካባቢ የተገኙት ሰነዶች ይህን ቃል መጥቀሳቸው የሐዋርያት ሥራ ዘገባ ትክክል እንደሆነ ያረጋግጣል፤ ከእነዚህ ሰነዶች አንዳንዶቹ የተዘጋጁት በመጀመሪያው መቶ ዘመን ዓ.ዓ. ነው።
-