የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • “መናገርህን ቀጥል እንጂ ዝም አትበል”
    ‘ስለ አምላክ መንግሥት በሚገባ መመሥከር’
    • 8, 9. ጳውሎስ ለአይሁዳውያን በትጋት መስበኩ የመረረ ተቃውሞ ሲያስከትልበት ምን አደረገ? ከዚያ በኋላስ ለመስበክ ወዴት ሄደ?

      8 ሲላስና ጢሞቴዎስ ከመቄዶንያ የተለያዩ ስጦታዎችን ይዘው መጡ፤ ጳውሎስ በዚህ ጊዜ ያደረገው ነገር በግልጽ እንደሚያሳየው ሰብዓዊ ሥራ ይሠራ የነበረው አገልግሎቱን ሲያከናውን ኑሮውን ለመደጎም እንዲያግዘው ብቻ ነው። (2 ቆሮ. 11:9) ዘገባው እንደሚገልጸው ጳውሎስ ወዲያውኑ “ቃሉን በመስበኩ ሥራ በእጅጉ ተጠመደ [“በማስተማር ጊዜውን ሁሉ ያሳልፍ ነበር፣” የ1980 ትርጉም]።” (ሥራ 18:5) ይሁን እንጂ ይህ የስብከት እንቅስቃሴ ከአይሁዳውያን ዘንድ የመረረ ተቃውሞ ገጠመው። ጳውሎስ ስለ ክርስቶስ የሚገልጸውን ሕይወት አድን መልእክት ለመቀበል አሻፈረኝ በማለታቸው ከዚያ በኋላ በኃላፊነት እንደማይጠየቅ ለማሳየት ልብሱን አራገፈ፤ እንዲህም አላቸው፦ “ደማችሁ በራሳችሁ ላይ ይሁን። እኔ ንጹሕ ነኝ። ከአሁን ጀምሮ ወደ አሕዛብ እሄዳለሁ።”—ሥራ 18:6፤ ሕዝ. 3:18, 19

  • “መናገርህን ቀጥል እንጂ ዝም አትበል”
    ‘ስለ አምላክ መንግሥት በሚገባ መመሥከር’
    • 10. ጳውሎስ ከአሕዛብ ወገን ለሆኑ ሰዎች ብቻ ለመስበክ ወስኖ እንዳልነበር የሚያሳየው ምንድን ነው?

      10 ጳውሎስ “ከአሁን ጀምሮ ወደ አሕዛብ እሄዳለሁ” ማለቱ አይሁዳውያንንም ሆነ ወደ ይሁዲነት የተለወጡትን ሰዎች ጨርሶ እንደተዋቸው የሚያሳይ ነው? መልእክቱን ለመቀበል ፈቃደኛ ለሚሆኑት እንኳ ትኩረት አይሰጥም ማለት ነው? ይህ ሊሆን አይችልም። ለምሳሌ ያህል፣ “የምኩራብ አለቃው ቀርስጶስ ከቤተሰቡ ሁሉ ጋር በጌታ አመነ” የሚል ዘገባ እናነባለን። ከሁኔታው መረዳት እንደሚቻለው በምኩራቡ ይሰበሰቡ ከነበሩት ሰዎች መካከል ብዙዎች ቀርስጶስ የወሰደው ዓይነት እርምጃ ወስደዋል፤ ምክንያቱም መጽሐፍ ቅዱስ “መልእክቱን የሰሙ በርካታ የቆሮንቶስ ሰዎችም አምነው ይጠመቁ ጀመር” ይላል። (ሥራ 18:8) በመሆኑም በቆሮንቶስ የተቋቋመው አዲስ ጉባኤ በቲቶስ ኢዮስጦስ ቤት መሰብሰብ ጀመረ። ሉቃስ ይህን ዘገባ የጻፈው እንደተለመደው በጊዜ ቅደም ተከተል ከሆነ እነዚህ አይሁዳውያንም ሆኑ ወደ ይሁዲነት የተለወጡ ሰዎች ክርስትናን የተቀበሉት ጳውሎስ ልብሱን ካራገፈ በኋላ ነው። ይህም ስለ ሐዋርያው የሚነግረን ቁም ነገር አለ፤ ጳውሎስ ምሥራቹን ሲሰብክ እንደ ሁኔታው ማስተካከያ የሚያደርግ ሰው ነበር።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ