-
“መናገርህን ቀጥል እንጂ ዝም አትበል”‘ስለ አምላክ መንግሥት በሚገባ መመሥከር’
-
-
“በዚህች ከተማ ብዙ ሰዎች አሉኝ” (የሐዋርያት ሥራ 18:9-17)
12. ጳውሎስ በራእይ ምን ማረጋገጫ ተሰጠው?
12 ጳውሎስ በቆሮንቶስ አገልግሎቱን መቀጠል ይኖርበት እንደሆነና እንዳልሆነ ጥያቄ ተፈጥሮበት ይሆን? ከሆነም ጌታ ኢየሱስ ሌሊት በራእይ ሲገለጥለት መልሱን ሊያገኝ ነው፤ እንዲህ አለው፦ “አትፍራ፤ መናገርህን ቀጥል እንጂ ዝም አትበል፤ እኔ ከአንተ ጋር ስለሆንኩ ማንም አንተን ሊያጠቃና ሊጎዳህ አይችልም፤ በዚህች ከተማ ብዙ ሰዎች አሉኝና።” (ሥራ 18:9, 10) እንዴት የሚያበረታታ ራእይ ነው! ጳውሎስ ምንም ጉዳት እንደማይደርስበት እንዲሁም ምሥራቹን መስማት የሚገባቸው ብዙ ሰዎች በከተማዋ ውስጥ እንዳሉ ጌታ ራሱ ማረጋገጫ ሰጠው። ታዲያ ጳውሎስ ለዚህ ራእይ ምን ምላሽ ሰጥቶ ይሆን? ዘገባው “በመካከላቸው የአምላክን ቃል እያስተማረ ለአንድ ዓመት ተኩል እዚያ ቆየ” ይላል።—ሥራ 18:11
-
-
“መናገርህን ቀጥል እንጂ ዝም አትበል”‘ስለ አምላክ መንግሥት በሚገባ መመሥከር’
-
-
16. ጌታ “መናገርህን ቀጥል እንጂ ዝም አትበል፤ እኔ ከአንተ ጋር [ነኝ]” በማለት የተናገረው ሐሳብ በአገልግሎታችን እንድንቀጥል የሚያበረታታን እንዴት ነው?
16 ጌታ ኢየሱስ ለጳውሎስ “አትፍራ፤ መናገርህን ቀጥል እንጂ ዝም አትበል፤ እኔ ከአንተ ጋር [ነኝ]” የሚል ማረጋገጫ የሰጠው አይሁዳውያን መልእክቱን አንቀበልም ካሉ በኋላ እንደነበር አስታውስ። (ሥራ 18:9, 10) እኛም በተለይ ሰዎች መልእክታችንን አልቀበል ሲሉን ይህን ሐሳብ ማስታወሳችን ጠቃሚ ነው። ይሖዋ ልብን እንደሚያነብና ቅን ልብ ያላቸውን ሰዎች ወደ ራሱ እንደሚስብ ፈጽሞ መዘንጋት የለብንም። (1 ሳሙ. 16:7፤ ዮሐ. 6:44) ይህ አገልግሎታችንን በትጋት ማከናወናችንን እንድንቀጥል የሚያበረታታ አይደለም? በየዓመቱ መቶ ሺዎች ይጠመቃሉ፤ በየቀኑ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ይጠመቃሉ ማለት ነው። “ከሁሉም ብሔራት ሰዎችን ደቀ መዛሙርት አድርጉ” የሚለውን ትእዛዝ እየፈጸሙ ላሉ ሁሉ ኢየሱስ “እኔ እስከ ሥርዓቱ መደምደሚያ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ” የሚል ዋስትና ሰጥቷል።—ማቴ. 28:19, 20
-