የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ‘ከሰው ሁሉ ደም ንጹሕ ነኝ’
    ‘ስለ አምላክ መንግሥት በሚገባ መመሥከር’
    • 12, 13. (ሀ) የአውጤኪስ ትንሣኤ በጉባኤው ላይ ምን ስሜት አሳድሯል? (ለ) በዛሬው ጊዜ የሚወዱትን ሰው በሞት ያጡ ሰዎች በየትኛው የመጽሐፍ ቅዱስ ተስፋ ይጽናናሉ?

      12 ጳውሎስና የጉዞ ጓደኞቹ መቄዶንያን አቋርጠው የተጓዙት አብረው ነው፤ ከዚያ ግን ለተወሰነ ጊዜ የተለያዩ ይመስላል። ከሁኔታው መረዳት እንደሚቻለው፣ የጉዞ ቡድኑ እንደገና የተሰባሰበው ጥሮአስ ላይ ነው።d ዘገባው እንዲህ ይላል፦ “በአምስት ቀን ጊዜ ውስጥም እነሱ ወዳሉበት ወደ ጥሮአስ ደረስን።”e (ሥራ 20:6) በዚህ ምዕራፍ መግቢያ ላይ የተጠቀሰው ወጣቱ አውጤኪስ ከሞት የተነሳው በጥሮአስ ነበር። በዚያ የነበሩት ክርስቲያኖች፣ የእምነት አጋራቸው አውጤኪስ ከሞት በመነሳቱ ምን ያህል ተደስተው እንደሚሆን አስበው! ዘገባው “እጅግ ተጽናኑ” ይላል።—ሥራ 20:12

  • ‘ከሰው ሁሉ ደም ንጹሕ ነኝ’
    ‘ስለ አምላክ መንግሥት በሚገባ መመሥከር’
    • d ሉቃስ የሐዋርያት ሥራ 20:5, 6 ላይ ያለውን ዘገባ ሲጽፍ በአንደኛ መደብ ተውላጠ ስም በመጠቀም ራሱንም ታሪኩ ውስጥ አካትቷል፤ ከዚህ መረዳት እንደሚቻለው፣ ጳውሎስ ቀደም ሲል ፊልጵስዩስ ላይ የተወውን ሉቃስን እዚያው ዳግም ያገኘው ይመስላል፤ ከዚያም አብረው ወደ ጥሮአስ ሄደዋል።—ሥራ 16:10-17, 40

      e ከፊልጵስዩስ ወደ ጥሮአስ ያደረጉት ጉዞ አምስት ቀን ፈጅቶባቸዋል። ከዚህ ቀደም ተመሳሳይ ጉዞ በሁለት ቀን ውስጥ አድርገው ነበር፤ ምናልባትም በዚህ ወቅት ለጉዞ የማይመች ነፋስ አጋጥሟቸው ሊሆን ይችላል።—ሥራ 16:11

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ