-
“የይሖዋ ፈቃድ ይሁን”‘ስለ አምላክ መንግሥት በሚገባ መመሥከር’
-
-
በሐዋርያት ሥራ 21:1-17 ላይ የተመሠረተ
1-4. ጳውሎስ ወደ ኢየሩሳሌም የሚጓዘው ለምንድን ነው? እዚያስ ምን ይጠብቀዋል?
ጳውሎስና ሉቃስ ከሚሊጢን በሚነሳው መርከብ ላይ ቆመዋል፤ ስንብቱ በጣም ከባድ ነበር። ከሚወዷቸው የኤፌሶን ሽማግሌዎች ጋር የተለያዩት በግድ ነው! አሁን ሁለቱ ሚስዮናውያን ጉዞ ሊጀምሩ ነው። ለጉዞ የሚያስፈልጓቸውን በርካታ ነገሮች ሸክፈዋል። ከዚህ በተጨማሪ በይሁዳ ላሉ ችግረኛ ክርስቲያኖች የተሰባሰበውን ገንዘብ ይዘዋል፤ ይህን ስጦታ በማስረከብ ኃላፊነታቸውን ለመወጣት ቸኩለዋል።
2 ነፋሱ የመርከቡን ሸራዎች ወጠራቸው፤ መርከቡም በጫጫታ የተሞላውን ወደብ ተሰናብቶ መንቀሳቀስ ጀመረ። እነዚህ ሁለት ሰዎችና ሰባቱ የጉዞ ጓደኞቻቸው፣ ዓይናቸው ከባሕሩ ዳርቻ አልተነቀለም፤ በሐዘን የተዋጡት ወንድሞቻቸው አሁንም እዚያው ናቸው። (ሥራ 20:4, 14, 15) መርከቡ ርቆ ወዳጆቻቸው ከዓይናቸው እስኪሰወሩ ድረስ መንገደኞቹ እጃቸውን ማውለብለባቸውን አላቆሙም።
-
-
“የይሖዋ ፈቃድ ይሁን”‘ስለ አምላክ መንግሥት በሚገባ መመሥከር’
-
-
5. ጳውሎስና የጉዞ ጓደኞቹ ወደ ጢሮስ የተጓዙት እንዴት ነው?
5 ጳውሎስና ጓደኞቹ የተሳፈሩበት መርከብ በዚያው ቀን ቆስ ደረሰ፤ ‘የተጓዘው በቀጥታ’ ነው። ተስማሚ ነፋስ ስለነበረ በዚያ እየተነዱ በፍጥነት መጓዝ ችለው ነበር። (ሥራ 21:1) መርከቡ ቆስ ላይ መልሕቁን ጥሎ ያደረ ይመስላል፤ በማግስቱ ወደ ሮድስ ከዚያም ወደ ጳጥራ ጉዞውን ቀጠለ። በትንሿ እስያ ደቡባዊ ዳርቻ ላይ ወደምትገኘው ጳጥራ ሲደርሱ ወንድሞች በአንድ ትልቅ የዕቃ ማጓጓዣ መርከብ ተሳፍረው በፊንቄ ወደምትገኘው ጢሮስ አመሩ። በጉዟቸው ላይ ‘የቆጵሮስን ደሴት በስተ ግራ ትተው’ አለፉ። (ሥራ 21:3) የሐዋርያት ሥራን የጻፈው ሉቃስ ይህን ጉዳይ ለይቶ የጠቀሰው ለምንድን ነው?
-