-
“የማቀርበውን የመከላከያ መልስ ስሙ”‘ስለ አምላክ መንግሥት በሚገባ መመሥከር’
-
-
11. ሽማግሌዎቹ ለጳውሎስ ምን ምክር ሰጡት? ሆኖም ጳውሎስ ለማድረግ ፈቃደኛ የሚሆናቸው ወይም የማይሆናቸው ነገሮች ምንድን ናቸው? (የግርጌ ማስታወሻውንም ተመልከት።)
11 በጳውሎስ ላይ የተወራው ነገር ትክክል ባይሆንም አይሁዳውያን ክርስቲያኖች በሰሙት ነገር ተረብሸዋል። በመሆኑም ሽማግሌዎቹ እንዲህ የሚል ምክር ሰጡት፦ “ስእለት ያለባቸው አራት ሰዎች በእኛ ዘንድ አሉ። እነዚህን ሰዎች ይዘህ በመሄድ ከእነሱ ጋር የመንጻት ሥርዓት ፈጽም፤ ራሳቸውንም እንዲላጩ የሚያስፈልገውን ገንዘብ ክፈልላቸው። ይህን ካደረግክ በአንተ ላይ የተወራው ሁሉ ከንቱ መሆኑንና አንተም ሕጉን እያከበርክ በሥርዓት እንደምትኖር ሁሉም ሰው ያውቃል።”c—ሥራ 21:23, 24
12. ጳውሎስ የኢየሩሳሌም ሽማግሌዎች ምክር ሲሰጡት እሺ ባይና ተባባሪ መሆኑን ያሳየው እንዴት ነው?
12 ጳውሎስ የችግሩ ዋና መንስኤ ስለ እሱ የተወራው አሉባልታ ሳይሆን አይሁዳውያን አማኞች ለሙሴ ሕግ ያላቸው ቅንዓት እንደሆነ በመግለጽ መቃወም ይችል ነበር። ይሁን እንጂ አምላክ ያወጣቸው መሠረታዊ ሥርዓቶች እስካልተጣሱ ድረስ ሽማግሌዎቹ ያሉትን ለማድረግ ፈቃደኛ ሆኗል። ቀደም ሲል “እኔ ራሴ በሕግ ሥር ባልሆንም እንኳ በሕግ ሥር ያሉትን እማርክ ዘንድ በሕግ ሥር ላሉት በሕግ ሥር እንዳለሁ ሆንኩ” በማለት ጽፎ ነበር። (1 ቆሮ. 9:20) በዚህ ወቅት ጳውሎስ ከኢየሩሳሌም ሽማግሌዎች ጋር በመተባበር “በሕግ ሥር” እንዳለ ሆኗል። ከሽማግሌዎች ጋር በመተባበርና እኔ ያልኩት ካልሆነ ብሎ ድርቅ ከማለት በመቆጠብ ረገድ ግሩም ምሳሌ ትቶልናል።—ዕብ. 13:17
ጳውሎስ ቅዱስ ጽሑፋዊ መሠረታዊ ሥርዓቶች እስካልተጣሱ ድረስ የሌሎችን ሐሳብ ይቀበል ነበር። አንተስ?
-
-
“የማቀርበውን የመከላከያ መልስ ስሙ”‘ስለ አምላክ መንግሥት በሚገባ መመሥከር’
-
-
c አንዳንድ ምሁራን፣ እነዚህ ሰዎች የናዝራዊነት ስእለት እንደነበረባቸው ይናገራሉ። (ዘኁ. 6:1-21) እርግጥ ነው፣ ይህን ስእለት የሚያካትተው የሙሴ ሕግ አሁን ተሽሯል። ይሁንና እነዚህ ሰዎች የተሳሉት ለይሖዋ በመሆኑ ጳውሎስ ስእለቱን መፈጸማቸው ስህተት እንዳልሆነ አስቦ ሊሆን ይችላል። በመሆኑም የሰዎቹን ወጪ መክፈሉና አብሯቸው መሄዱ ምንም ስህተት የለውም። ሰዎቹ የተሳሉት ምን ዓይነት ስእለት እንደሆነ በእርግጠኝነት ማወቅ አንችልም። ይሁንና ብዙውን ጊዜ ናዝራውያን ከኃጢአት ለመንጻት የእንስሳት መሥዋዕት ያቀርቡ እንደነበር ይታወቃል፤ የሰዎቹ ስእለት ምንም ዓይነት ይሁን፣ ጳውሎስ እንዲህ ያለውን መሥዋዕት ለማቅረብ እንደማይስማማ ጥያቄ የለውም። ፍጹም የሆነው የክርስቶስ መሥዋዕት ከቀረበ ወዲህ የእንስሳት መሥዋዕቶች ኃጢአትን ማስተሰረይ አይችሉም። ጳውሎስ ያደረገው ነገር ምንም ይሁን ምን፣ ሕሊናውን የሚያስጥስ ነገር ለማድረግ እንደማይስማማ እርግጠኞች መሆን እንችላለን።
-