-
‘በናፍቆት መጠባበቅ’መጠበቂያ ግንብ—1998 | መስከረም 15
-
-
“የፍጥረት ናፍቆት”
12, 13. ሰብዓዊ ፍጥረት ‘ለከንቱነት የተገዛው’ እንዴት ነው? ሌሎች በጎችስ የሚናፍቁት ምንን ነው?
12 ሌሎች በጎች በናፍቆት የሚጠባበቁት ነገር አላቸውን? በእርግጥ አላቸው። ይሖዋ በመንፈስ የተወለዱ “ልጆቹ” እንዲሆኑና በሰማያዊ መንግሥት ‘ከክርስቶስ ጋር አብረው እንዲወርሱ’ የመረጣቸው ሰዎች ስላላቸው ክብራማ ተስፋ ከተናገረ በኋላ ጳውሎስ እንዲህ አለ:- “የፍጥረት ናፍቆት የእግዚአብሔርን ልጆች መገለጥ ይጠባበቃልና። ፍጥረት ለከንቱነት ተገዝቶአልና፣ በተስፋ ስላስገዛው ነው እንጂ በፈቃዱ አይደለም፤ ተስፋውም ፍጥረት ራሱ ደግሞ ከጥፋት ባርነት ነፃነት ወጥቶ ለእግዚአብሔር ልጆች ወደሚሆን ክብር ነፃነት እንዲደርስ ነው።”—ሮሜ 8:14–21፤ 2 ጢሞቴዎስ 2:10–12
-
-
‘በናፍቆት መጠባበቅ’መጠበቂያ ግንብ—1998 | መስከረም 15
-
-
14. ‘የአምላክ ልጆች መገለጥ’ ምን ነገር የሚጨምር ይሆናል? ይህ ‘የሰው ልጆችን ከጥፋት ባርነት ነፃ የሚያወጣውስ’ እንዴት ይሆናል?
14 በመጀመሪያ የተቀቡት ‘የአምላክ ልጆች’ ቀሪዎች ‘መገለጥ’ አለባቸው። ይህ ምንን ይጨምራል? አምላክ የወሰነው ጊዜ ሲደርስ ቅቡዓኑ ከክርስቶስ ጋር ለመንገሥ ‘መታተማቸውና’ ክብር መጎናጸፋቸው ለሌሎች በጎች ግልጽ ይሆናል። (ራእይ 7:2–4) በተጨማሪም ከሞት የተነሡት ‘የአምላክ ልጆች’ ከክርስቶስ ጋር በመሆን የሰይጣንን ክፉ የነገሮች ሥርዓት በማጥፋቱ እርምጃ ተካፋይ በመሆን ‘ይገለጣሉ።’ (ራእይ 2:26, 27፤ 19:14, 15) ከዚያም በክርስቶስ የሺህ ዓመት ግዛት ወቅት የኢየሱስን ቤዛዊ መሥዋዕት ጥቅሞች ለሰብዓዊው “ፍጥረት” የሚያድሉ ክህነታዊ መስመሮች በመሆን ‘ይገለጣሉ።’ ይህም የሰው ልጆችን ‘ከጥፋት ባርነት ነፃ በማውጣት’ “ለእግዚአብሔር ልጆች ወደሚሆን ክብር ነፃነት” እንዲገቡ ያደርጋቸዋል። (ሮሜ 8:21፤ ራእይ 20:5፤ 22:1, 2) ሌሎች በጎች እነዚህን የመሳሰሉ ታላላቅ ተስፋዎች ከፊታቸው ተዘርግተውላቸው እያሉ “የእግዚአብሔርን ልጆች መገለጥ” ‘በናፍቆት ቢጠባበቁ’ ያስደንቃል?—ሮሜ 8:19
-