-
አምላክ ክፋት እንዲቀጥል በመፍቀዱ ምን ተምረናል?እውነተኛውን አንድ አምላክ አምልክ
-
-
8. ጳውሎስ የትኞቹን ነጥቦች እንድናጤን አሳስቦናል?
8 ሐዋርያው ጳውሎስ በሮሜ ለሚገኙ ክርስቲያኖች በጻፈው ደብዳቤ ላይ “እግዚአብሔር አድልዎ ያደርጋልን?” የሚል ጥያቄ ካቀረበ በኋላ “በፍጹም አያደርግም!” ሲል በእርግጠኝነት መልስ ሰጥቷል። ከዚያም የአምላክን ምሕረት ጎላ አድርጎ የገለጸ ሲሆን ይሖዋ ፈርዖን ለተወሰነ ጊዜ እንዲቀጥል የፈቀደበትን ምክንያት አስመልክቶ የተናገረውን ቃልም ጠቅሷል። በተጨማሪም ጳውሎስ እኛ የሰው ልጆች በሸክላ ሠሪ እጅ እንዳለ ሸክላ እንደሆንን አመልክቷል። አክሎም እንዲህ ሲል ተናግሯል:- “እግዚአብሔር ቍጣውን ለማሳየት፣ ኀይሉንም ለማሳወቅ ፈልጎ የቍጣው መግለጫ [“ዕቃዎች፣” የ1954 ትርጉም] የሆኑትን፣ ለጥፋትም የተዘጋጁትን እጅግ ታግሦ ቢሆንሳ! አስቀድሞ ለክብር ላዘጋጃቸው፣ የምሕረቱም መግለጫዎች [“ዕቃዎች፣” የ1954 ትርጉም] ለሆኑት፣ የክብሩ ባለ ጠግነት እንዲታወቅ ይህን አድርጎ እንደ ሆነስ? የጠራው ከአይሁድ ወገን ብቻ ሳይሆን ከአሕዛብ ወገን የሆ[ን]ነውን እኛን እንኳ ሳይቀር አይደለምን?”—ሮሜ 9:14-24
-
-
አምላክ ክፋት እንዲቀጥል በመፍቀዱ ምን ተምረናል?እውነተኛውን አንድ አምላክ አምልክ
-
-
10. ይሖዋ ላለፉት 1,900 ዓመታት ክፉዎችን የታገሠው ለምንድን ነው?
10 ኢየሱስ ከሞት ከተነሳበት ጊዜ አንስቶ ከ1,900 ለሚበልጡ ዓመታት ይሖዋ ‘በቁጣ ዕቃዎች’ ላይ የጥፋት እርምጃ ከመውሰድ በመታቀብ ተጨማሪ ትዕግሥት አሳይቷል። ለምን? አንደኛው ምክንያት በሰማያዊው መንግሥት ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር የሚገዙትን ለመሰብሰብ ሲል ነው። እነዚህ ሰዎች ቁጥራቸው 144,000 ሲሆን ሐዋርያው ጳውሎስ ‘የምሕረት ዕቃዎች’ ሲል ጠርቷቸዋል። መጀመሪያ የዚህ ሰማያዊ ክፍል አባላት እንዲሆኑ የተጠሩት አይሁዳውያን ነበሩ። ከጊዜ በኋላ አምላክ ከአሕዛብ ወገን ለሆኑ ሰዎችም ይህን ጥሪ አቅርቧል። ይሖዋ እነዚህ ሰዎች እንዲያገለግሉት አላስገደዳቸውም። ከዚህ ይልቅ ፍቅራዊ ዝግጅቶቹን ከሚያደንቁ ሰዎች መካከል የተወሰኑት በሰማያዊው መንግሥት ከልጁ ጋር ተባባሪ ገዥዎች የመሆን መብት እንዲያገኙ አድርጓል። አሁን የዚህን ሰማያዊ ክፍል አባላት የመሰብሰቡ ሥራ ተገባዷል።—ሉቃስ 22:29፤ ራእይ 14:1-4
-