-
“ለማንም ክፉን በክፉ አትመልሱ”መጠበቂያ ግንብ—2007 | ሐምሌ 1
-
-
“አትበቀሉ”
15. በሮሜ 12:19 ላይ ከመበቀል እንድንርቅ የሚያነሳሳን ምን ምክንያት ተገልጿል?
15 ጳውሎስ መበቀል የሌለብን ለምን እንደሆነ የሚያሳይ ሌላ አሳማኝ ማስረጃ ሰጥቶናል፤ ብድራት አለመመለስ ትሑቶች እንደሆንን ያሳያል። “ወዳጆቼ ሆይ፤ ለእግዚአብሔር ቊጣ ፈንታ ስጡ እንጂ አትበቀሉ፤ ‘በቀል የእኔ ነው፤ እኔ ብድራትን እመልሳለሁ’ ይላል ጌታ ተብሎ ተጽፎአልና” ብሏል። (ሮሜ 12:19) ለመበቀል የሚሞክር ክርስቲያን ትዕቢተኛ ነው። እንዲህ ማድረግ አምላክ ሊወስደው የሚገባውን እርምጃ እርሱ መውሰድ ይሆንበታል። (ማቴዎስ 7:1) ከዚህም በላይ ለደረሰበት ነገር የአጸፋ እርምጃ መውሰዱ ይሖዋ “እኔ ብድራትን እመልሳለሁ” በማለት በሰጠው ማረጋገጫ ላይ እምነት እንደሌለው ያሳያል። ከዚህ በተቃራኒ እውነተኛ ክርስቲያኖች ይሖዋ ‘ለምርጦቹ እንደሚፈርድላቸው’ ይተማመናሉ። (ሉቃስ 18:7, 8፤ 2 ተሰሎንቄ 1:6-8) አምላክ እንዲበቀልላቸው ጉዳዩን ለእርሱ በመተው ትሑቶች መሆናቸውን ያሳያሉ።—ኤርምያስ 30:23, 24፤ ሮሜ 1:18
-
-
“ለማንም ክፉን በክፉ አትመልሱ”መጠበቂያ ግንብ—2007 | ሐምሌ 1
-
-
18. አጸፋ ከመመለስ መቆጠብ ትክክለኛ እንዲሁም ፍቅርና ትሕትና የሚንጸባረቅበት እርምጃ ነው የምንለው ለምንድን ነው?
18 በሮሜ ምዕራፍ 12 ላይ ባደረግነው አጠር ያለ ምርምር ‘ለማንም ክፉን በክፉ ከመመለስ’ እንድንቆጠብ የሚያደርጉንን በርካታ ምክንያቶች ተመልክተናል። በመጀመሪያ፣ አጸፋ ከመመለስ መቆጠብ ልንከተለው የሚገባ ትክክለኛ አካሄድ ነው። አምላክ ካሳየን ርኅራኄ አንጻር ራሳችንን ለአምላክ መሥዋዕት አድርገን ማቅረባችንና ጠላቶቻችንን እንድንወድ የተሰጠንን ትእዛዝ ጨምሮ ሌሎች መመሪያዎቹን በፈቃደኝነት መታዘዛችን ትክክልና ምክንያታዊ ነው። ሁለተኛ፣ ክፉን በክፉ ከመመለስ መራቃችን ፍቅር የሚንጸባረቅበት አካሄድ ነው። አጸፋ ከመመለስ በመቆጠብና ሰላም በማስፈን አንዳንዶችን ሌላው ቀርቶ ኃይለኛ ተቃዋሚዎች የነበሩ ሰዎችንም እንኳ የይሖዋ አምላኪ እንደሚሆኑ ተስፋ በማድረግ በፍቅር ልንረዳቸው እንችላለን። ሦስተኛ፣ ክፉን በክፉ አለመመለሳችን ትሑቶች እንደሆንን ያሳያል። ይሖዋ “በቀል የእኔ ነው” ስላለ ራሳችን ለመበቀል መሞከር መታበይ ይሆናል። ከዚህም በተጨማሪ የአምላክ ቃል “ትዕቢት ስትመጣ ውርደትም ትከተላለች፤ በትሑት ዘንድ ግን ጥበብ ትገኛለች” በማለት ያስጠነቅቃል። (ምሳሌ 11:2) በደል ሲደርስብን አምላክ እንዲበቀልልን ጉዳዩን በጥበብ ለእርሱ በመተው ትሑቶች እንደሆንን እናሳያለን።
-