-
የክርስቶስን አስተሳሰብ አንጸባርቁመጠበቂያ ግንብ—2000 | መስከረም 1
-
-
4, 5. በሮሜ 15:1-3 ላይ ጎላ ተደርጎ የተገለጸው የትኛው የኢየሱስ አስተሳሰብ ገጽታ ነው? ክርስቲያኖች እርሱን መምሰል የሚችሉት እንዴት ነው?
4 የክርስቶስ ኢየሱስን አስተሳሰብ መያዝ ምን ነገሮችን ይጨምራል? ሐዋርያው ጳውሎስ ለሮሜ ክርስቲያኖች የጻፈው ደብዳቤ 15ኛ ምዕራፍ ለዚህ ጥያቄ መልስ እንድናገኝ ይረዳናል። ጳውሎስ የዚህ ምዕራፍ መክፈቻ በሆኑት ጥቂት ቁጥሮች ላይ አንዱን የኢየሱስ ጉልህ ባሕርይ ጠቅሷል። እንዲህ አለ:- “እኛም ኃይለኞች [“ብርቱዎች፣” የ1980 ትርጉም ] የሆንን የደካሞችን ድካም እንድንሸከም ራሳችንንም ደስ እንዳናሰኝ ይገባናል። እያንዳንዳችን እንድናንጸው እርሱን ለመጥቀም ባልንጀራችንን ደስ እናሰኝ። ክርስቶስ ራሱን ደስ አላሰኘምና፤ ነገር ግን:- አንተን የነቀፉበት ነቀፋ ወደቀብኝ ተብሎ እንደ ተጻፈ ሆነበት።”—ሮሜ 15:1-3
-
-
የክርስቶስን አስተሳሰብ አንጸባርቁመጠበቂያ ግንብ—2000 | መስከረም 1
-
-
6. ኢየሱስ ተቃውሞና ነቀፋ ሲደርስበት የሰጠውን ምላሽ ልንኮርጅ የምንችለው እንዴት ነው?
6 ኢየሱስ ያንጸባረቀው ሌላው ጉልህ ባሕርይ ደግሞ ሁልጊዜ ገንቢ የሆነው አስተሳሰቡና ድርጊቱ ነው። ሌሎች ሰዎች የነበራቸው አፍራሽ አስተሳሰብ አምላክን ለማገልገል በነበረው መልካም አስተሳሰብ ላይ ተጽዕኖ እንዲያሳድርበት ፈጽሞ አልፈቀደም። እኛም ተጽዕኖ እንዲያሳድርብን መፍቀድ አይኖርብንም። ኢየሱስ አምላክን በታማኝነት በማገልገሉ ምክንያት ነቀፋና ስደት በደረሰበት ጊዜ ያለ ምንም ማማረር በትዕግሥት ጸንቷል። ‘የሚያንጸውን ነገር በማድረግ’ ባልንጀራቸውን ለማስደሰት የሚጣጣሩ ሁሉ እምነትና አስተዋይነት ከጎደለው ዓለም ተቃውሞ ሊደርስባቸው እንደሚችል ያውቅ ነበር።
7. ኢየሱስ ትዕግሥት ያሳየው እንዴት ነው? እኛም እንዲሁ ማድረግ ያለብን ለምንድን ነው?
7 ኢየሱስ በሌሎች መንገዶችም ትክክለኛ የሆነ አስተሳሰብ አሳይቷል። ይሖዋ ዓላማዎቹን ደረጃ በደረጃ የሚፈጽምበትን ጊዜ በትዕግሥት ተጠባብቋል። (መዝሙር 110:1፤ ማቴዎስ 24:36፤ ሥራ 2:32-36፤ ዕብራውያን 10:12, 13) በተጨማሪም ኢየሱስ ተከታዮቹን በትዕግሥት ይዟቸዋል። “ከእኔም ተማሩ” ብሏቸዋል። “የዋህ” እንደመሆኑ መጠን የሚሰጠው መመሪያ የሚያንጽና መንፈስን የሚያድስ ነበር። እንዲሁም ‘በልቡ ትሑት’ ስለሆነ ራሱን ከልክ በላይ ከፍ ከፍ የሚያደርግ ወይም ዕብሪተኛ አልነበረም። (ማቴዎስ 11:29) ጳውሎስ የሚከተለውን በተናገረ ጊዜ እነዚህን የኢየሱስ አስተሳሰብ ገጽታዎች እንድንመስል አበረታቶናል:- “በክርስቶስ ኢየሱስ የነበረ ይህ አሳብ በእናንተ ዘንድ ደግሞ ይሁን። እርሱ በእግዚአብሔር መልክ ሲኖር ሳለ ከእግዚአብሔር ጋር መተካከልን መቀማት እንደሚገባ ነገር አልቈጠረውም፣ ነገር ግን የባሪያን መልክ ይዞ በሰውም ምሳሌ ሆኖ ራሱን ባዶ አደረገ።”—ፊልጵስዩስ 2:5-7
8, 9. (ሀ) ከራስ ወዳድነት ነፃ የሆነ አስተሳሰብ ለማዳበር ጥረት ማድረግ ያለብን ለምንድን ነው? (ለ) ኢየሱስ የተወልንን ምሳሌ ፍጹም በሆነ መንገድ መከተል ቢያቅተን ተስፋ መቁረጥ የማይኖርብን ለምንድን ነው? በዚህ ረገድ ጳውሎስ ጥሩ ምሳሌ የሚሆነው እንዴት ነው?
8 ሌሎችን ማገልገልና ከራሳችን ፍላጎት ይልቅ የእነርሱን ፍላጎት ማስቀደም እንዳለብን መናገሩ ቀላል ነው። ይሁን እንጂ አስተሳሰባችንን በሃቀኝነት በምንመረምርበት ጊዜ ልባችን ሙሉ በሙሉ ከዚያ አባባል ጋር አለመጣጣሙን እንገነዘብ ይሆናል። ይህ የሚሆነው ለምንድን ነው? አንደኛ የራስ ወዳድነት ባሕርያትን ከአዳምና ከሔዋን በመውረሳችን ሲሆን ሁለተኛ ደግሞ የራስ ወዳድነት ምኞትን በሚያራምድ ዓለም ውስጥ የምንኖር በመሆናችን ነው። (ኤፌሶን 4:17, 18) ከራስ ወዳድነት ነፃ የሆነ አስተሳሰብ ማዳበር ማለት አብሮን ከተወለደው ፍጽምና የጎደለው ባሕርይ ተቃራኒ የሆነ አስተሳሰብ ማዳበር ማለት ነው። ይህ ደግሞ ቁርጥ ያለ እርምጃ መውሰድንና ጥረት ማድረግን ይጠይቃል።
-