የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • የአምላክ መንግሥት ምንድን ነው?
    ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
    • 7. የአምላክ መንግሥት ሰዎች ከሚያስተዳድሩት ከየትኛውም መንግሥት የላቁ ሕጎች አሉት

      መንግሥታት ለዜጎቻቸው ጥቅምና ጥበቃ ያስገኛሉ ብለው የሚያስቧቸውን ሕጎች ያወጣሉ። የአምላክ መንግሥትም ተገዢዎቹ ሊያከብሯቸው የሚገቡ ሕጎች አሉት። አንደኛ ቆሮንቶስ 6:9-11⁠ን አንብቡ፤ ከዚያም በሚከተሉት ጥያቄዎች ላይ ተወያዩ፦

      • ሁሉም ሰው አምላክ ያወጣቸውን የሥነ ምግባር ደንቦች ቢከተል ዓለማችን ምን መልክ የሚኖራት ይመስልሃል?a

      • ይሖዋ የመንግሥቱ ተገዢዎች እነዚህን ሕጎች እንዲያከብሩ መጠበቁ ምክንያታዊ ይመስልሃል? እንዲህ ብለህ የመለስከው ለምንድን ነው?

      • እነዚህን ሕጎች የማይታዘዙ ሰዎች ሊለወጡ እንደሚችሉ የሚያሳይ ምን ማስረጃ አለ?—ቁጥር 11⁠ን ተመልከት።

      ብዙ ሰዎች በሚተላለፉበት መንገድ ላይ ትራፊኩን እያስተናበረ ያለ ፖሊስ። የተለያየ ዕድሜ ያላቸው ሰዎች መንገዱን እያቋረጡ ነው

      መንግሥታት ለዜጎቻቸው ጥበቃና ጥቅም የሚያስገኙ የተለያዩ ሕጎችን ያወጣሉ። የአምላክ መንግሥት ለተገዢዎቹ ጥበቃና ጥቅም የሚያስገኙ የላቁ ሕጎች አሉት

  • መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ፆታ ግንኙነት ምን ይላል?
    ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
    • ይሖዋ ለእኛ የተሻለው ነገር ምን እንደሆነ ያውቃል። የሥነ ምግባር ንጽሕናችንን መጠበቅ የምንችለው እንዴት እንደሆነና እንዲህ ማድረጋችን ምን ጥቅም እንደሚያስገኝልን ገልጾልናል። ምሳሌ 7:7-27⁠ን አንብቡ ወይም ቪዲዮውን ተመልከቱ፤ ከዚያም በሚከተሉት ጥያቄዎች ላይ ተወያዩ፦

      ቪዲዮ፦ በማስተዋል ተመላለሱ (9:31)

      • እዚህ ጥቅስ ላይ ያለው ወጣት ራሱን ፈተና ውስጥ ያስገባው እንዴት ነው?—ምሳሌ 7:8, 9⁠ን ተመልከት።

      • ምሳሌ 7:23, 26 ላይ እንደተገለጸው የፆታ ብልግና መፈጸም አስከፊ መዘዝ ሊያስከትል ይችላል። የሥነ ምግባር ንጽሕናችንን መጠበቃችን ከየትኞቹ ችግሮች ያድነናል?

      • የሥነ ምግባር ንጽሕናችንን መጠበቃችን ለዘላለም በደስታ ለመኖር የሚያስችለን እንዴት ነው?

      አንዳንድ ሰዎች መጽሐፍ ቅዱስ ግብረ ሰዶምን አስመልክቶ የሚናገረው ሐሳብ ፍቅር የጎደለው እንደሆነ ይሰማቸዋል። ሆኖም አፍቃሪ አምላክ የሆነው ይሖዋ ሁሉም ሰው ለዘላለም በደስታ እንዲኖር ይፈልጋል። እንዲህ ዓይነት ሕይወት ማግኘት ከፈለግን ከእሱ መሥፈርቶች ጋር ተስማምተን መኖር አለብን። አንደኛ ቆሮንቶስ 6:9-11⁠ን አንብቡ፤ ከዚያም በሚከተለው ጥያቄ ላይ ተወያዩ፦

      • በዚህ ጥቅስ መሠረት በአምላክ ዘንድ ተቀባይነት የሌለው ግብረ ሰዶም ብቻ ነው?

      አምላክን ለማስደሰት ሁላችንም የተለያዩ ለውጦች ማድረግ ያስፈልገናል። በዚህ ረገድ የምናደርገው ጥረት የሚያስቆጭ ነው? መዝሙር 19:8, 11⁠ን አንብቡ፤ ከዚያም በሚከተሉት ጥያቄዎች ላይ ተወያዩ፦

      • ይሖዋ ያወጣቸው የሥነ ምግባር መሥፈርቶች ምክንያታዊ ወይም ተገቢ ይመስሉሃል? እንዲህ ብለህ የመለስከው ለምንድን ነው?

      1. በሐዘን የተዋጠች አንዲት ወጣት ከወንድ ጓደኛዋ አጠገብ ተቀምጣ። ከጓደኞቿ ጋር የምሽት ክበብ ውስጥ ሆና እየጠጣችና እያጨሰች ነው 2. ያቺው ሴት በስብሰባ አዳራሽ ውስጥ ከእህቶች ጋር በደስታ ስታወራ

      ይሖዋ ብዙዎች እሱ ካወጣቸው የሥነ ምግባር መሥፈርቶች ጋር ተስማምተው መኖር እንዲችሉ ረድቷል። አንተንም ሊረዳህ ይችላል

  • ክርስቲያኖች ለአልኮል መጠጥ ምን አመለካከት ሊኖራቸው ይገባል?
    ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
    • 6. ከልክ በላይ የመጠጣት ልማድን ማሸነፍ

      ከልክ በላይ ይጠጣ የነበረ አንድ ሰው ይህን ልማድ እንዲያሸንፍ የረዳው ምንድን ነው? ቪዲዮውን ተመልከቱ፤ ከዚያም በሚከተሉት ጥያቄዎች ላይ ተወያዩ፦

      ቪዲዮ፦ ‘በሕይወቴ ተመረርኩ’ (6:32)

      ‘በሕይወቴ ተመረርኩ’ ከሚለው ቪዲዮ ላይ የተወሰዱ ትዕይንቶች፦ 1. ዲሚትሪ የአልኮል መጠጥ የያዘ ጠርሙስ ሲያይ 2. ዲሚትሪ፣ ባለቤቱና ሴት ልጃቸው መጽሐፍ ቅዱስን አብረው ሲያነብቡ
      • በቪዲዮው ላይ ዲሚትሪ የአልኮል መጠጥ ሲጠጣ ምን ዓይነት ጠባይ ያሳይ ነበር?

      • የመጠጥ ሱሱን ወዲያው ማሸነፍ ችሏል?

      • በመጨረሻም ከአልኮል መጠጥ ሱስ መላቀቅ የቻለው እንዴት ነው?

      አንደኛ ቆሮንቶስ 6:10, 11⁠ን አንብቡ፤ ከዚያም በሚከተሉት ጥያቄዎች ላይ ተወያዩ፦

      • ስካር እንደ ቀላል የሚታይ ጉዳይ ነው?

      • ከልክ በላይ የአልኮል መጠጥ ይጠጣ የነበረ ሰው ሊለወጥ ይችላል የምንለው ለምንድን ነው?

      ማቴዎስ 5:30⁠ን አንብቡ፤ ከዚያም በሚከተለው ጥያቄ ላይ ተወያዩ፦

      • ‘እጅን መቁረጥ’ የሚለው አገላለጽ ይሖዋን ለማስደሰት ሲሉ መሥዋዕትነት መክፈልን ያመለክታል። የመጠጥ ሱስን ለማሸነፍ እየታገልክ ከሆነ ምን ማድረግህ ይረዳሃል?a

      አንደኛ ቆሮንቶስ 15:33⁠ን አንብቡ፤ ከዚያም በሚከተለው ጥያቄ ላይ ተወያዩ፦

      • ብዙ ከሚጠጡ ሰዎች ጋር ጓደኛ መሆንህ ምን ጉዳት ይኖረዋል?

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ