-
የጌታ እራት ለአንተ ትርጉም የሚኖረው ለምንድን ነው?መጠበቂያ ግንብ—1993 | መጋቢት 15
-
-
የሐዋርያው ጳውሎስ ቃላት ስለ ክርስቶስ ሞት የመታሰቢያ በዓል ማብራሪያ ይሰጡናል። “ለእናንተ ደግሞ አሳልፌ የሰጠሁትን እኔ ከጌታ ተቀብያለሁና፤ ጌታ ኢየሱስ አልፎ በተሰጠባት በዚያች ሌሊት እንጀራን አንስቶ አመሰገነ፣ ቆርሶም:- እንካችሁ ብሉ፤ ይህ ስለ እናንተ የሚሆን ሥጋዬ [ማለት አዓት] ነው። ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት አለ። እንደዚሁም ከእራት በኋላ ጽዋውን ደግሞ አንስቶ ይህ ጽዋ በደሜ የሚሆን አዲስ ኪዳን ነው። በጠጣችሁት ጊዜ ሁሉ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት አለ። ይህን እንጀራ በበላችሁ ጊዜ ሁሉ፣ ይህንም ጽዋ በጠጣችሁ ጊዜ ሁሉ ጌታ እስኪመጣ ድረስ ሞቱን ትናገራላችሁና።” — 1 ቆሮንቶስ 11:23–26
-
-
የጌታ እራት ለአንተ ትርጉም የሚኖረው ለምንድን ነው?መጠበቂያ ግንብ—1993 | መጋቢት 15
-
-
በዓሉ የሚከበረው በስንት በስንት ጊዜ ነው?
ሐዋርያው ጳውሎስ “ይህን እንጀራ በበላችሁ ጊዜ ሁሉ፣ ይህንም ጽዋ በጠጣችሁ ጊዜ ሁሉ ጌታ እስኪመጣ ድረስ ሞቱን ትናገራላችሁና” ሲል የተናገራቸው ቃላት ትርጉም ምንድን ነው? ታማኝ የሆኑ ቅቡዓን ክርስቲያኖች እስኪሞቱ ድረስ ከመታሰቢያው ምሳሌያዊ ቂጣና ወይን ጠጅ ደጋግመው ይካፈላሉ ማለት ነው። ከሞቱ በኋላ ግን ሰማያዊ ሕይወት አግኝተው ይነሳሉ። ከቂጣውና ከወይን ጠጁ በተካፈሉ ቁጥር ይሖዋ በኢየሱስ መሥዋዕት አማካኝነት ባዘጋጀው ቤዛ ላይ እምነት ያላቸው መሆኑን በአምላክና በዓለም ፊት ይናገራሉ ወይም ያውጃሉ። ይህን የሚያደርጉት እስከመቼ ድረስ ነው? ጳውሎስ “ጌታ እስኪመጣ ድረስ” በማለት ተናግሮአል። የዚህ በዓል አከባበር ኢየሱስ ቅቡዓን ተከታዮቹን ከሙታን አስነስቶ በሰማይ እስከሚቀበልበት እስከ “መገኘቱ” ዘመን ድረስ ነው ማለቱ እንደነበረ ግልጽ ነው። (1 ተሰሎንቄ 4:14–17) ይህም ክርስቶስ ለአስራ አንዱ ታማኝ አገልጋዮቹ ከተናገረው ከሚከተለው ቃል ጋር ይስማማል። “እኔ ባለሁበት እናንተ ደግሞ እንድትሆኑ ሁለተኛ እመጣለሁ ወደ እኔም እወስዳችኋለሁ።” — ዮሐንስ 14:3
የክርስቶስ ሞት በየቀኑ ወይም በየሳምንቱ መከበር ይኖርበታልን? ኢየሱስ የጌታን እራት አከባበር ያቋቋመውና የተገደለው እስራኤላውያን ከግብጽ ባርነት የወጡበት ቀን ይታሰብበት በነበረው የማለፍ ቀን ነው። እንዲያውም ኢየሱስ ለክርስቲያኖች የተሰዋ በግ ስለሆነ “ፋሲካችን ክርስቶስ” ተብሎአል። (1 ቆሮንቶስ 5:7) የፋሲካ ወይም የማለፍ በዓል ይከበር የነበረው በየዓመቱ አንድ ጊዜ ኒሳን 14 ቀን ላይ ነበር። (ዘጸአት 12:6, 14፤ ዘሌዋውያን 23:5) ይህም የኢየሱስ ሞት በየቀኑ ወይም በየሳምንቱ ሳይሆን እንደ ፋሲካ ወይም እንደ ማለፍ በዓል በዓመት አንድ ጊዜ ብቻ መከበር እንደሚኖርበት ያመለክታል።
ክርስቲያን ነን ይሉ የነበሩ ሰዎች ለብዙ መቶ ዓመታት የኢየሱስን ሞት ያስቡ የነበረው በዓመት አንድ ጊዜ ነበር። ያከብሩ የነበረውም ኒሳን 14 ቀን ስለነበረ ኳርቶዴሲማንስ ወይም 14ተኛ ቀን አክባሪዎች ተብለው ይጠሩ ነበር። ታሪክ ፀሐፊው ጄ ኤል ፎን ሞስሃይም ስለእነዚህ ሰዎች ሲጽፉ እንዲህ ብለዋል:- “የታናሽቱ እስያ ክርስቲያኖች ይህን የጌታ እራትና የኢየሱስ ክርስቶስ ሞት መታሰቢያ የሆነውን ቅዱስ እራት የሚያከብሩት አይሁዳውያን የፋሲካ ወይም የማለፍ በጋቸውን በሚበሉት ጊዜ ማለትም በመጀመሪያው ወር [ኒሳን]፣ በወሩ አሥራ አራተኛ ቀን ምሽት ነበር። . . . ክርስቶስ የተወዉ ምሳሌ የሕግን ያህል የአስገዳጅነት ኃይል እንዳለው ያምኑ ነበር።”
-