-
“ሙታን ይነሣሉ”መጠበቂያ ግንብ—1998 | ሐምሌ 1
-
-
7. (ሀ) ጳውሎስ ትኩረቱን ያደረገው በየትኛው ቁልፍ ነጥብ ላይ ነበር? (ለ) ከሞት የተነሣውን ኢየሱስ እነማን አይተውታል?
7 ጳውሎስ በ1 ቆሮንቶስ ምዕራፍ 15 የመጀመሪያ ሁለት ቁጥሮች ላይ የንግግሩን ጭብጥ ገልጿል:- “ወንድሞች ሆይ፣ የሰበክሁላችሁን ደግሞም የተቀበላችሁትን በእርሱም ደግሞ የቆማችሁበትን በእርሱም ደግሞ የምትድኑበትን ወንጌል አሳስባችኋለሁ፤ በከንቱ ካላመናችሁ በቀር።” የቆሮንቶስ ሰዎች በምሥራቹ ጸንተው ካልቆሙ እውነትን የተቀበሉት በከንቱ ነው። ጳውሎስ በመቀጠል እንዲህ አለ:- “እኔ ደግሞ የተቀበልሁትን ከሁሉ በፊት አሳልፌ ሰጠኋችሁ እንዲህ ብዬ:- መጽሐፍ እንደሚል ክርስቶስ ስለ ኃጢአታችን ሞተ፣ ተቀበረም፣ መጽሐፍም እንደሚል በሦስተኛው ቀን ተነሣ፣ ለኬፋም ታየ በኋላም ለአሥራ ሁለቱ፤ ከዚያም በኋላ ከአምስት መቶ ለሚበዙ ወንድሞች በአንድ ጊዜ ታየ፤ ከእነርሱም የሚበዙቱ እስከ አሁን አሉ አንዳንዶች ግን አንቀላፍተዋል፤ ከዚያም በኋላ ለያዕቆብ ኋላም ለሐዋርያት ሁሉ ታየ፤ ከሁሉም በኋላ እንደ ጭንጋፍ ለምሆን ለእኔ ደግሞ ታየኝ።”—1 ቆሮንቶስ 15:3-8
-
-
“ሙታን ይነሣሉ”መጠበቂያ ግንብ—1998 | ሐምሌ 1
-
-
9 በተጨማሪም ክርስቶስ ብዙ ሰዎችን ላቀፈ ቡድን ማለትም “ከአምስት መቶ ለሚበዙ ወንድሞች” ታይቷል። ኢየሱስ ይህን ያህል ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ተከታዮች የነበሩት በገሊላ ስለነበር ድርጊቱ የተፈጸመው በማቴዎስ 28:16-20 ላይ ተዘግቦ በሚገኘው መሠረት ኢየሱስ ደቀ መዛሙርት አድርጉ የሚለውን ትእዛዝ በሰጠበት ወቅት መሆን አለበት። እነዚህ ግለሰቦች የሚሰጡት የምሥክርነት ቃል ምንኛ አሳማኝ ይሆን! ጳውሎስ ይህን የመጀመሪያ ደብዳቤ ለቆሮንቶስ ሰዎች በጻፈበት በ55 እዘአ ላይም አንዳንዶቹ በሕይወት ነበሩ። እነዚያ የሞቱት ግን “አንቀላፍተዋል” እንደተባለላቸው ልብ በል። ሰማያዊ ሽልማታቸውን ለመቀበል ገና አልተነሡም ነበር።
-