የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ትንሣኤ—አስተማማኝ ተስፋ!
    መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2020 | ታኅሣሥ
    • 12. በ1 ጴጥሮስ 3:18, 22 መሠረት የኢየሱስ ትንሣኤ ከዚያ ቀደም ከተከናወኑት ትንሣኤዎች የሚለየው እንዴት ነው?

      12 ጳውሎስ ‘ክርስቶስ ከሞት እንደተነሳ’ በእርግጠኝነት ያውቅ ነበር። የኢየሱስ ትንሣኤ ከዚያ ቀደም ከተከናወኑት ትንሣኤዎች የላቀ ነበር፤ ምክንያቱም ከሞት የተነሱት ሌሎቹ ሰዎች በድጋሚ ሞተዋል። ኢየሱስ “በሞት ካንቀላፉት በኩራት ሆኖ” ከሞት እንደተነሳ ጳውሎስ ተናግሯል። ኢየሱስ በኩራት የተባለው ከምን አንጻር ነው? መንፈሳዊ አካል ይዞ ከሞት ለመነሳትም ሆነ ከሞት ከተነሳ በኋላ ወደ ሰማይ ለመሄድ የመጀመሪያው ሰው እሱ ነው።—1 ቆሮ. 15:20፤ ሥራ 26:23፤ 1 ጴጥሮስ 3:18, 22⁠ን አንብብ።

  • ትንሣኤ—አስተማማኝ ተስፋ!
    መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2020 | ታኅሣሥ
    • 16. ጳውሎስ ኢየሱስን “በኩራት” ብሎ መጥራቱ ምን ያመለክታል?

      16 ጳውሎስ “ክርስቶስ በሞት ካንቀላፉት በኩራት ሆኖ ከሞት ተነስቷል” በማለት ጽፏል። እርግጥ ነው፣ አልዓዛርን ጨምሮ ሌሎች ሰዎች ከሞት ተነስተው በምድር ላይ ኖረዋል፤ ሆኖም መንፈስ ሆኖ ከሞት ለመነሳትና የዘላለም ሕይወት ለማግኘት የመጀመሪያው ሰው ኢየሱስ ነበር። ኢየሱስ፣ እስራኤላውያን ለአምላክ ያቀርቡ ከነበረው የፍሬ በኩራት ጋር ሊመሳሰል ይችላል። በተጨማሪም ጳውሎስ ኢየሱስን “በኩራት” ብሎ መጥራቱ ከእሱ በኋላ ሌሎች ሰዎችም ከሞት ተነስተው ሰማያዊ ሕይወት እንደሚያገኙ ይጠቁማል። ሐዋርያትን ጨምሮ ‘ከክርስቶስ ጋር አንድነት ያላቸው’ ሌሎች ሰዎች ከጊዜ በኋላ የኢየሱስ ዓይነት ትንሣኤ ያገኛሉ።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ