-
የኢየሱስ ትንሣኤ የዘላለም ሕይወት ያስገኛል!መጠበቂያ ግንብ—2013 | መጋቢት 1
-
-
የኢየሱስ ትንሣኤ በዛሬው ጊዜ ላለነው ሰዎች ትርጉም የሌለው በጥንት ጊዜ የተፈጸመ አንድ ክስተት ብቻ አይደለም። ሐዋርያው ጳውሎስ እንደሚከተለው በማለት በጻፈ ጊዜ ትንሣኤው ያለውን ጠቀሜታ ገልጿል፦ “ክርስቶስ በሞት ካንቀላፉት በኩራት ሆኖ ከሞት ተነስቷል። ሞት የመጣው በአንድ ሰው በኩል ስለሆነ የሙታን ትንሣኤም በአንድ ሰው በኩል ነው። ምክንያቱም ሁሉም በአዳም እንደሚሞቱ ልክ እንደዚሁም ሁሉም በክርስቶስ ሕያው ይሆናሉ።”—1 ቆሮንቶስ 15:20-22
-
-
የኢየሱስ ትንሣኤ የዘላለም ሕይወት ያስገኛል!መጠበቂያ ግንብ—2013 | መጋቢት 1
-
-
ጳውሎስ በመቀጠል የተናገረው ሐሳብም በኢየሱስ ትንሣኤ አማካኝነት የሚፈጸሙ ነገሮችን ይገልጻል። “ሞት የመጣው በአንድ ሰው በኩል ስለሆነ የሙታን ትንሣኤም በአንድ ሰው በኩል ነው” ብሏል። ከአዳም በወረስነው ኃጢአትና አለፍጽምና ምክንያት ሁላችንም እንሞታለን። ይሁን እንጂ ኢየሱስ ፍጹም ሰብዓዊ ሕይወቱን ቤዛ አድርጎ በመስጠት የሰው ዘር በትንሣኤ አማካኝነት ከኃጢአትና ከሞት ነፃ የሚወጣበትን መንገድ ከፍቷል። ጳውሎስ በሮም 6:23 ላይ እንዲህ በማለት ጉዳዩን ጥሩ አድርጎ ገልጾታል፦ “ኃጢአት የሚከፍለው ደሞዝ ሞት ነው፤ አምላክ የሚሰጠው ስጦታ ግን በጌታችን በክርስቶስ ኢየሱስ የዘላለም ሕይወት ነው።”
-