-
“እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ይወዳል”መጠበቂያ ግንብ—1998 | ኅዳር 1
-
-
ጳውሎስ እንደ መቄዶንያ ርቀው ለሚገኙ ጉባኤዎች ሳይቀር የእርዳታ ጥሪ ያቀረበ ሲሆን በይሁዳ ለሚኖሩ ችግር ለደረሰባቸው ክርስቲያኖች የገንዘብ መዋጮ እንዲደረግ ዝግጅት አድርጓል። ለቆሮንቶስ ክርስቲያኖች እንዲህ ሲል ጽፎላቸዋል:- “ለገላትያ አብያተ ክርስቲያናት እንደ ደነገግሁት እናንተ ደግሞ እንዲሁ አድርጉ። . . . ከእናንተ እያንዳንዱ በየሳምንቱ በፊተኛው ቀን እንደ ቀናው መጠን እያስቀረ በቤቱ ያስቀምጥ።”a—1 ቆሮንቶስ 16:1, 2
-
-
“እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ይወዳል”መጠበቂያ ግንብ—1998 | ኅዳር 1
-
-
a ምንም እንኳ ጳውሎስ “እንደ ደነገግሁት” ብሎ ቢናገርም፣ በራሱ አነሳሽነት የግድ እንዲያዋጡ ደንግጓል ማለት አይደለም። ከዚህ ይልቅ በርካታ ጉባኤዎች የሚያደርጉትን መዋጮ በበላይነት ይቆጣጠር ነበር ማለት ነው። ከዚህም በተጨማሪ ጳውሎስ እያንዳንዱ ሰው “በቤቱ” የሚሰጠው “እንደ ቀናው መጠን” እንዲሆን ተናግሯል። በሌላ አነጋገር ማንኛውም መዋጮ የሚደረገው በግል፣ በራስ አነሳሽነት ነበር። ማንም ሰው መዋጮ እንዲያደርግ አይገደድም ነበር።
-