-
ሥራችሁ እሳቱን ይቋቋም ይሆን?መጠበቂያ ግንብ—1998 | ኅዳር 1
-
-
በትክክለኛ የግንባታ ቁሳቁስ ተጠቅሞ ማነጽ
9. ጳውሎስ ዋነኛ ሥራው መሠረት መጣል ቢሆንም እሱ ያስተማረውን እውነት ለተቀበሉ ሰዎች እንደሚያስብላቸው ያሳየው እንዴት ነበር?
9 ጳውሎስ እንዲህ ሲል ጽፏል:- “ማንም ግን በዚህ መሠረት ላይ በወርቅ ቢሆን በብርም በከበረ ድንጋይም በእንጨትም በሣርም ወይም በአገዳ ቢያንጽ፣ የእያንዳንዱ ሥራ ይገለጣል፤ በእሳት ስለሚገለጥ ያ ቀን ያሳያልና፣ የእያንዳንዱም ሥራ እንዴት መሆኑን እሳቱ ይፈትነዋል።” (1 ቆሮንቶስ 3:12, 13) ጳውሎስ ምን ማለቱ ነበር? ይህን የተናገረበትን ምክንያት ተመልከቱ። የጳውሎስ ተቀዳሚ ተግባር መሠረት መጣል ነበር። ባደረጋቸው የሚስዮናዊ ጉዞዎች ከከተማ ወደ ከተማ በመጓዝ ስለ ክርስቶስ ሰምተው ለማያውቁ ብዙ ሰዎች ሰብኳል። (ሮሜ 15:20) ሰዎች የሚያስተምረውን እውነት ሲቀበሉ ጉባኤዎች ይመሠረቱ ነበር። ጳውሎስ ለእነዚህ የታመኑ ሰዎች ከልብ ያስብ ነበር። (2 ቆሮንቶስ 11:28, 29) ይሁን እንጂ ሥራው ከቦታ ወደ ቦታ መዘዋወርን ይጠይቅበት ነበር። ስለዚህ በቆሮንቶስ መሠረት በመጣል 18 ወራት ያህል ከቆየ በኋላ በሌሎች ከተሞች ለመስበክ ሄደ። ያም ሆኖ ግን እሱ ጀምሮት የሄደውን የስብከት ሥራ ሌሎች እንዴት እያከናወኑት እንዳሉ ለማወቅ ይፈልግ ነበር።—ሥራ 18:8–11፤ 1 ቆሮንቶስ 3:6
10, 11. (ሀ) ጳውሎስ ለግንባታ የሚያገለግሉ ሁለት ዓይነት ቁሳቁሶችን ያነጻጸረው እንዴት ነው? (ለ) በጥንቷ ቆሮንቶስ ቃል በቃል ምን ዓይነት ሕንፃዎች ኖረው ሊሆን ይችላል? (ሐ) በአብዛኛው እሳትን ሊቋቋሙ የሚችሉ ሕንፃዎች ምን ዓይነት ናቸው? ይህስ ደቀ መዛሙርት በማድረጉ ሥራ ለሚካፈሉ ሰዎች ምን ግሩም ትምህርት ይሰጣል?
10 ጳውሎስ በቆሮንቶስ በጣለው መሠረት ላይ እየገነቡ የነበሩ አንዳንድ ሰዎች መናኛ የሆነ ሥራ እየሠሩ ነበር። ችግሩን በግልጽ ለማስቀመጥ እንዲያመች ሲል ጳውሎስ ሁለት ዓይነት የግንባታ ቁሳቁስ ማለትም ወርቅን፣ ብርንና የከበረ ድንጋይን ከእንጨት፣ ከሣርና ከአገዳ ጋር አነጻጽሯል። አንድ ሕንፃ ግሩም በሆኑ፣ ረዥም ጊዜ በሚቆዩና እሳትን መቋቋም በሚችሉ ነገሮች ሊገነባ ይችላል፤ አሊያም ደግሞ ዘላቂነት በሌላቸው፣ ጊዜያዊና እሳት መቋቋም በማይችሉ ቁሳቁሶች መገንባት ይቻላል። እንደ ቆሮንቶስ የመሳሰሉ ትላልቅ ከተሞች በሁለቱም ዓይነት የግንባታ ቁሳቁሶች የተገነቡ ሕንፃዎች በብዛት እንደሚኖሯቸው አያጠራጥርም። ግዙፍና ውድ ከሆኑ ጥርብ ድንጋዮች የተሠሩና ምናልባትም በፊት ለፊት በኩል ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል በወርቅና በብር ያጌጡ አስደናቂ ቤተ መቅደሶች ነበሩ።b እነዚህ ጠንካራ መሠረት ያላቸው ሕንጻዎች በአጠገባቸው ከሚገኙት ከእንጨት ከተሠሩና የሣር ክዳን ካላቸው ደሳሳ ቤቶች እንዲሁም የገበያ ዳሶች በላይ ገዝፈውና ተውበው ሳይታዩ አይቀርም።
-
-
ሥራችሁ እሳቱን ይቋቋም ይሆን?መጠበቂያ ግንብ—1998 | ኅዳር 1
-
-
12. አንዳንድ የቆሮንቶስ ክርስቲያኖች ግዴለሽነት የሚታይበት የግንባታ ሥራ በማከናወን ላይ የነበሩት በምን መንገዶች ነው?
12 በግልጽ ለማየት እንደሚቻለው ጳውሎስ በቆሮንቶስ የሚገኙ አንዳንድ ክርስቲያኖች መናኛ የሆኑ ግንባታዎችን እያካሄዱ እንዳሉ ተሰምቶት ነበር። ችግሩ ምን ነበር? የጥቅሱ ሐሳብ እንደሚያሳየው የጉባኤውን አንድነት አደጋ ላይ የሚጥል ቢሆንም እንኳ የሰዎችን ስብዕና በሚያወድሱ ግለሰቦች ጉባኤው ተከፋፍሎ ነበር። አንዳንዶች “እኔ የጳውሎስ ነኝ” ሲሉ ሌሎች ደግሞ “እኔስ የአጵሎስ ነኝ” ይሉ ነበር። አንዳንዶች በራሳቸው ጥበብ ከሚገባው በላይ ተመክተው የነበሩ ይመስላል። በውጤቱም የሥጋዊ አስተሳሰብ አየር እንዲሰፍን፣ መንፈሳዊ ጉልምስና እንዳይኖር እንዲሁም “ቅናትና ክርክር” እንዲበራከት ማድረጉ ምንም አያስደንቅም። (1 ቆሮንቶስ 1:12፤ 3:1–4, 18) እነዚህ አስተሳሰቦች በጉባኤና በአገልግሎት በሚሰጡ ትምህርቶች ላይ እንደሚንጸባረቁ አያጠራጥርም። በመሆኑም መናኛ በሆኑ ቁሳቁሶች እንደሚሠራ የግንባታ ሥራ ደቀ መዛሙርት የማድረጉ ሥራቸው ግዴለሽነት የሚታይበት ነበር። ‘እሳቱን’ ሊቋቋም የማይችል ነበር። ጳውሎስ እዚህ ላይ የተናገረው እሳት ምንድን ነው?
-
-
ሥራችሁ እሳቱን ይቋቋም ይሆን?መጠበቂያ ግንብ—1998 | ኅዳር 1
-
-
14. (ሀ) ክርስቲያን ደቀ መዛሙርት አድራጊዎች ‘ጉዳት ሊደርስባቸው’ የሚችለው እንዴት ሊሆን ይችላል? ሆኖም በእሳት ውስጥ እንዳለፉ ሆነው መዳንን ማግኘት የሚችሉት እንዴት ነው? (ለ) ሊገጥመን የሚችለውን ጉዳት መቀነስ የምንችለው እንዴት ነው?
14 በእርግጥም ሊጤን የሚገባው አነጋገር ነው! አንድ ሰው ደቀ መዝሙር እንዲሆን ለመርዳት ብዙ ከደከምን በኋላ ግለሰቡ በፈተና ወይም በስደት ሲሸነፍ ብሎም ከእውነት መንገድ ሲወጣ መመልከት እጅግ የሚያሳዝን ሊሆን ይችላል። ጳውሎስም ቢሆን እንዲህ ዓይነት ነገር መድረሱ ለገነባው ሰው ጉዳት መሆኑን ሲናገር ይህንኑ መግለጹ ነበር። ሁኔታው የሚያስከትልብን ሥቃይ ከፍተኛ ሊሆን ስለሚችል መዳናችን “በእሳት [“ውስጥ አልፎ፣” NW] እንደሚድን” ሰው ተደርጎ ተገልጿል። ይህም ንብረቱ ሁሉ ተቃጥሎበት ሕይወቱ ብቻ ከተረፈለት ሰው ጋር ሊመሳሰል ይችላል። እኛ በበኩላችን የዚህ ዓይነቱን አሳዛኝ ሁኔታ መከሰት መቀነስ የምንችለው እንዴት ነው? ጠንካራ በሆኑ ቁሳቁሶች በመገንባት ነው! ተማሪዎቻችንን ልባቸውን በሚነካ መንገድ ካስተማርናቸውና እንደ ጥበብ፣ ማስተዋል፣ ይሖዋን መፍራትና እውነተኛ እምነት ማሳየት የመሳሰሉ ውድ ክርስቲያናዊ ባሕርያትን ከፍ አድርገው እንዲመለከቱ የምናበረታታቸው ከሆነ ጠንካራ በሆኑና እሳትን መቋቋም በሚችሉ ቁሳቁሶች እየገነባን ነው ማለት ነው። (መዝሙር 19:9, 10፤ ምሳሌ 3:13–15፤ 1 ጴጥሮስ 1:6, 7) እነዚህን ባሕርያት ያዳበሩ ሰዎች የአምላክን ፈቃድ በማድረግ ይቀጥላሉ፤ እርግጠኛ የሆነው ለዘላለም ሕያው ሆኖ የመኖር ተስፋ የእነሱ ይሆናል። (1 ዮሐንስ 2:17) ሆኖም የጳውሎስን ምሳሌ ተግባራዊ ልናደርግ የምንችለው እንዴት ነው? አንዳንድ ምሳሌዎችን ተመልከቱ።
15. የመጽሐፍ ቅዱስ ተማሪዎቻችንን በተመለከተ የግዴለሽነት የግንባታ ሥራ ከማከናወን ልንርቅ የምንችለው በምን መንገዶች ነው?
15 የመጽሐፍ ቅዱስ ተማሪዎቻችንን በምናስተምርበት ጊዜ ትኩረታቸው ከይሖዋ አምላክ ይልቅ ወደ ሰዎች እንዲሆን ማድረግ አይገባም። ግባችን የጥበብ ምንጭ እኛ እንደሆን አድርገው እንዲመለከቱ ማስተማር መሆን የለበትም። መመሪያ ለማግኘት ወደ ይሖዋ፣ ወደ ቃሉና ወደ ድርጅቱ ዘወር እንዲሉ እንፈልጋለን። በመሆኑም ለሚጠይቁን ጥያቄዎች የራሳችንን አስተያየት ከመስጠት እንቆጠባለን። ከዚህ ይልቅ መጽሐፍ ቅዱስንና “ታማኝና ልባም ባሪያ” የሚያዘጋጃቸውን ጽሑፎች በመጠቀም መልሶችን እንዴት ማግኘት እንደሚችሉ እናስተምራቸዋለን። (ማቴዎስ 24:45–47) በተመሳሳይም የመጽሐፍ ቅዱስ ተማሪዎቻችን ከእኛ ጋር ባላቸው ግንኙነት ብቻ እንዲወሰኑ ማድረግ የለብንም። ጥናቶቻችንን ሌሎች ሊቀርቧቸው ሲሞክሩ ቅር ከመሰኘት ይልቅ ጥናቶቻችን ራሳቸው ፍቅራቸውን ‘በማስፋት’ በተቻለ መጠን በጉባኤው ውስጥ ካሉት ወንድሞች ጋር እንዲተዋወቁና እንዲቀራረቡ ልናበረታታቸው ይገባል።—2 ቆሮንቶስ 6:12, 13
16. ሽማግሌዎች እሳትን መቋቋም በሚችሉ ነገሮች ሊገነቡ የሚችሉት እንዴት ነው?
16 ክርስቲያን ሽማግሌዎችም ደቀ መዛሙርትን በመገንባቱ ሥራ ቁልፍ ሚና ይጫወታሉ። በጉባኤ ፊት ቆመው በሚያስተምሩበት ጊዜ እሳትን ሊቋቋሙ በሚችሉ ቁሳቁሶች ለመገንባት ይጥራሉ። የማስተማር ችሎታቸው፣ ተሞክሯቸውና ባሕርያቸው ይለያይ ይሆናል፤ ሆኖም እነዚህን ልዩነቶች በመጠቀም ተከታዮች ለማፍራት አይጥሩም። (ከሥራ 20:29, 30 ጋር አወዳድር።) በቆሮንቶስ ይገኙ የነበሩ አንዳንዶች “እኔ የጳውሎስ ነኝ” ወይም “እኔስ የአጵሎስ ነኝ” ይሉ የነበረው ለምን እንደሆነ በትክክል አናውቅም። ሆኖም ከእነዚህ ታማኝ ሽማግሌዎች ውስጥ አንዳቸውም ቢሆኑ እንዲህ ያለውን ከፋፋይ አስተሳሰብ እንዳላስፋፉ እርግጠኞች ልንሆን እንችላለን። ጳውሎስ እንዲህ ባሉት የስሜት መግለጫዎች አልተታለለም፤ በጽኑ አውግዟቸዋል። (1 ቆሮንቶስ 3:5–7) በተመሳሳይም ዛሬ ያሉ ሽማግሌዎች በእረኝነት የሚጠብቁት “የእግዚአብሔርን መንጋ” መሆኑን አይዘነጉም። (1 ጴጥሮስ 5:2፣ በሰያፍ የጻፍነው እኛ ነን።) የማንም ሰው ንብረት አይደለም። ስለዚህ ሽማግሌዎች አንድ ሰው መንጋውንም ሆነ የሽማግሌዎችን አካል የመጫን አዝማሚያ እንዳይኖረው ከፍተኛ ጥንቃቄ ያደርጋሉ። ሽማግሌዎች ጉባኤውን ለማገልገል፣ ልብን ለመንካትና በግ መሰል ሰዎች ይሖዋን በሙሉ ነፍስ እንዲያገለግሉ ለመርዳት ቅን ፍላጎት ካላቸው እሳትን ሊቋቋሙ በሚችሉ ነገሮች ይገነባሉ።
17. ክርስቲያን ወላጆች እሳትን መቋቋም በሚችሉ ነገሮች ለመገንባት የሚጥሩት እንዴት ነው?
17 ይህ ጉዳይ ክርስቲያን ወላጆችንም በጥልቅ የሚያሳስብ ነው። ልጆቻቸው የዘላለም ሕይወት አግኝተው ለማየት በጣም ይጓጓሉ! ለዚህም ነው በአምላክ ቃል ውስጥ የሚገኙትን መሠረታዊ ሥርዓቶች በልጆቻቸው ልብ ውስጥ ‘ለመቅረጽ’ ጠንክረው የሚሠሩት። (ዘዳግም 6:6, 7 NW) ልጆቻቸው እውነትን እንዲያውቁላቸው ይፈልጋሉ፤ እውነት እንዲያው የመመሪያዎች ክምችት ወይም የእውነታዎች ስብስብ እንደሆነ አድርገው ሳይሆን የተሟላ፣ የሚክስና የሚያስደስት የሕይወት መንገድ መሆኑን እንዲገነዘቡ ይፈልጋሉ። (1 ጢሞቴዎስ 1:11) አፍቃሪ ወላጆች ልጆቻቸው የታመኑ የክርስቶስ ደቀ መዛሙርት እንዲሆኑላቸው እሳትን መቋቋም በሚችሉ ነገሮች በመጠቀም ለመገንባት ይጥራሉ። ልጆቻቸው ይሖዋ የሚጠላቸውን ባሕርያት እንደ አረም ነቅለው እንዲጥሉና እሱ የሚወዳቸውን ባሕርያት ደግሞ እንዲያዳብሩ በመርዳት ከልጆቻቸው ጋር በትእግሥት ይሠራሉ።—ገላትያ 5:22, 23
-