-
ይህ የመዳን ቀን ነው!መጠበቂያ ግንብ—1998 | ታኅሣሥ 15
-
-
12. የይሖዋ አምባሳደሮችና መልእክተኞች የትኛውን አስፈላጊ የሆነ አገልግሎት በማከናወን ላይ ይገኛሉ?
12 ለመዳን ከጳውሎስ ቃላት ጋር የሚስማማ ተግባር መፈጸም አለብን:- “[ከይሖዋ ጋር] አብረንም እየሠራን የእግዚአብሔርን ጸጋ በከንቱ እንዳትቀበሉ ደግሞ እንለምናለን፤ በተወደደ ሰዓት ሰማሁህ በመዳንም ቀን ረዳሁህ ይላልና፤ እነሆ፣ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ እነሆ፣ የመዳን ቀን አሁን ነው።” (2 ቆሮንቶስ 6:1, 2) የይሖዋ ቅቡዓን አምባሳደሮችና መልእክተኞቹ “ሌሎች በጎች” የሰማያዊ አባታቸውን ይገባናል የማይሉት ደግነት በከንቱ አይቀበሉም። (ዮሐንስ 10:16) በጥሩ ምግባራቸውና ቅንዓት በተሞላው አገልግሎታቸው በዚህ “የተወደደ ሰዓት” መለኮታዊ ተቀባይነት ለማግኘት ይጥራሉ፤ እንዲሁም ለምድር ነዋሪዎች ይህ “የመዳን ቀን” መሆኑን በማሳወቅ ላይ ናቸው።
-
-
ይህ የመዳን ቀን ነው!መጠበቂያ ግንብ—1998 | ታኅሣሥ 15
-
-
15. መንፈሳዊ እስራኤላውያን ይገባናል ለማይሉት የአምላክ ደግነት ብቁ መሆናቸውን ለማረጋገጥ ጥረት ያደረጉት ከመቼ ጀምሮ ነበር? ከምንስ ዓላማ ጋር?
15 ጳውሎስ፣ ኢሳይያስ 49:8 ለቅቡዓን ክርስቲያኖች እንደሚሠራ በማመልከት አምላክ በሰጠው በዚህ “የተወደደ ሰዓት” እና “የመዳን ቀን” መልካም ፈቃዱን ባለመሻት ‘ይገባናል የማይሉትን የአምላክ ደግነት በከንቱ እንዳይቀበሉ’ ተማጽኗቸዋል። ጳውሎስ በማከል:- “እነሆ፣ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ እነሆ፣ የመዳን ቀን አሁን ነው።” (2 ቆሮንቶስ 6:2) በ33 እዘአ ከዋለው የጰንጠቆስጤ ቀን ጀምሮ መንፈሳዊ እስራኤላውያን “የተወደደው ሰዓት” “የመዳን ቀን” እንዲሆንላቸው ይገባናል የማይሉትን የአምላክ ደግነት ለመቀበል ብቁ መሆናቸውን ለማረጋገጥ ጥረት አድርገዋል።
-