የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ይህ የመዳን ቀን ነው!
    መጠበቂያ ግንብ—1998 | ታኅሣሥ 15
    • 12. የይሖዋ አምባሳደሮችና መልእክተኞች የትኛውን አስፈላጊ የሆነ አገልግሎት በማከናወን ላይ ይገኛሉ?

      12 ለመዳን ከጳውሎስ ቃላት ጋር የሚስማማ ተግባር መፈጸም አለብን:- “[ከይሖዋ ጋር] አብረንም እየሠራን የእግዚአብሔርን ጸጋ በከንቱ እንዳትቀበሉ ደግሞ እንለምናለን፤ በተወደደ ሰዓት ሰማሁህ በመዳንም ቀን ረዳሁህ ይላልና፤ እነሆ፣ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ እነሆ፣ የመዳን ቀን አሁን ነው።” (2 ቆሮንቶስ 6:​1, 2) የይሖዋ ቅቡዓን አምባሳደሮችና መልእክተኞቹ “ሌሎች በጎች” የሰማያዊ አባታቸውን ይገባናል የማይሉት ደግነት በከንቱ አይቀበሉም። (ዮሐንስ 10:​16) በጥሩ ምግባራቸውና ቅንዓት በተሞላው አገልግሎታቸው በዚህ “የተወደደ ሰዓት” መለኮታዊ ተቀባይነት ለማግኘት ይጥራሉ፤ እንዲሁም ለምድር ነዋሪዎች ይህ “የመዳን ቀን” መሆኑን በማሳወቅ ላይ ናቸው።

  • ይህ የመዳን ቀን ነው!
    መጠበቂያ ግንብ—1998 | ታኅሣሥ 15
    • 15. መንፈሳዊ እስራኤላውያን ይገባናል ለማይሉት የአምላክ ደግነት ብቁ መሆናቸውን ለማረጋገጥ ጥረት ያደረጉት ከመቼ ጀምሮ ነበር? ከምንስ ዓላማ ጋር?

      15 ጳውሎስ፣ ኢሳይያስ 49:​8 ለቅቡዓን ክርስቲያኖች እንደሚሠራ በማመልከት አምላክ በሰጠው በዚህ “የተወደደ ሰዓት” እና “የመዳን ቀን” መልካም ፈቃዱን ባለመሻት ‘ይገባናል የማይሉትን የአምላክ ደግነት በከንቱ እንዳይቀበሉ’ ተማጽኗቸዋል። ጳውሎስ በማከል:- “እነሆ፣ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ እነሆ፣ የመዳን ቀን አሁን ነው።” (2 ቆሮንቶስ 6:​2) በ33 እዘአ ከዋለው የጰንጠቆስጤ ቀን ጀምሮ መንፈሳዊ እስራኤላውያን “የተወደደው ሰዓት” “የመዳን ቀን” እንዲሆንላቸው ይገባናል የማይሉትን የአምላክ ደግነት ለመቀበል ብቁ መሆናቸውን ለማረጋገጥ ጥረት አድርገዋል።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ