-
ይህ የመዳን ቀን ነው!መጠበቂያ ግንብ—1998 | ታኅሣሥ 15
-
-
12. የይሖዋ አምባሳደሮችና መልእክተኞች የትኛውን አስፈላጊ የሆነ አገልግሎት በማከናወን ላይ ይገኛሉ?
12 ለመዳን ከጳውሎስ ቃላት ጋር የሚስማማ ተግባር መፈጸም አለብን:- “[ከይሖዋ ጋር] አብረንም እየሠራን የእግዚአብሔርን ጸጋ በከንቱ እንዳትቀበሉ ደግሞ እንለምናለን፤ በተወደደ ሰዓት ሰማሁህ በመዳንም ቀን ረዳሁህ ይላልና፤ እነሆ፣ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ እነሆ፣ የመዳን ቀን አሁን ነው።” (2 ቆሮንቶስ 6:1, 2) የይሖዋ ቅቡዓን አምባሳደሮችና መልእክተኞቹ “ሌሎች በጎች” የሰማያዊ አባታቸውን ይገባናል የማይሉት ደግነት በከንቱ አይቀበሉም። (ዮሐንስ 10:16) በጥሩ ምግባራቸውና ቅንዓት በተሞላው አገልግሎታቸው በዚህ “የተወደደ ሰዓት” መለኮታዊ ተቀባይነት ለማግኘት ይጥራሉ፤ እንዲሁም ለምድር ነዋሪዎች ይህ “የመዳን ቀን” መሆኑን በማሳወቅ ላይ ናቸው።
13. የኢሳይያስ 49:8 ፍሬ ነገር ምንድን ነው? የመጀመሪያ ፍጻሜውን ያገኘውስ እንዴት ነበር?
13 ጳውሎስ እንደሚከተለው የሚነበበውን ኢሳይያስ 49:8ን ጠቅሷል:- “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል:- በተወደደ ጊዜ ሰምቼሃለሁ፣ በመድኃኒትም ቀን ረድቼሃለሁ፤ እጠብቅህማለሁ፣ ምድርንም ታቀና ዘንድ፣ ውድማ የሆኑትንም ርስቶች ታወርስ ዘንድ፣ . . . ቃል ኪዳን አድርጌ ለሕዝቡ ሰጥቼሃለሁ።” ይህ ትንቢት በመጀመሪያ የተፈጸመው የእስራኤል ሕዝብ ከባቢሎን ምርኮ ነፃ ከወጡና ባድማ ወደ ሆነው የትውልድ ስፍራቸው በተመለሱ ጊዜ ነበር።—ኢሳይያስ 49:3, 9
14. ኢሳይያስ 49:8 ከኢየሱስ ጋር በተያያዘ ሁኔታ ፍጻሜ ያገኘው እንዴት ነበር?
14 የኢሳይያስ ትንቢት ተጨማሪ ፍጻሜውን ሲያገኝ ይሖዋ ‘አገልጋዩን’ ኢየሱስን “እስከ ምድር ዳር ድረስ መድኃኒት [ይ]ሆን ዘንድ [የአምላክ ማዳን ግልጥ ይሆን ዘንድ] ለአሕዛብ ብርሃን” አድርጎ ሰጥቷል። (ኢሳይያስ 49:6, 8፤ ከኢሳይያስ 42:1–4, 6, 7 እና ማቴዎስ 12:18–21 ጋር አወዳድር።) ‘የተወደደው ጊዜ’ ወይም “የተወደደው ሰዓት” ኢየሱስ በምድር ላይ የነበረበትን ጊዜ እንደሚያመለክት ግልጽ ነው። ኢየሱስ ጸልዮአል፤ አምላክም ‘ሰምቶታል።’ ይህ ፍጹም አቋሙን ለጠበቀው ለኢየሱስ “የመዳን ቀን” ሆኖለት ነበረ፤ ከዚህም የተነሣ “ለሚታዘዙለት ሁሉ የዘላለም መዳን ምክንያት [ሆኗል]።”—ዕብራውያን 5:7, 9፤ ዮሐንስ 12:27, 28
15. መንፈሳዊ እስራኤላውያን ይገባናል ለማይሉት የአምላክ ደግነት ብቁ መሆናቸውን ለማረጋገጥ ጥረት ያደረጉት ከመቼ ጀምሮ ነበር? ከምንስ ዓላማ ጋር?
15 ጳውሎስ፣ ኢሳይያስ 49:8 ለቅቡዓን ክርስቲያኖች እንደሚሠራ በማመልከት አምላክ በሰጠው በዚህ “የተወደደ ሰዓት” እና “የመዳን ቀን” መልካም ፈቃዱን ባለመሻት ‘ይገባናል የማይሉትን የአምላክ ደግነት በከንቱ እንዳይቀበሉ’ ተማጽኗቸዋል። ጳውሎስ በማከል:- “እነሆ፣ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ እነሆ፣ የመዳን ቀን አሁን ነው።” (2 ቆሮንቶስ 6:2) በ33 እዘአ ከዋለው የጰንጠቆስጤ ቀን ጀምሮ መንፈሳዊ እስራኤላውያን “የተወደደው ሰዓት” “የመዳን ቀን” እንዲሆንላቸው ይገባናል የማይሉትን የአምላክ ደግነት ለመቀበል ብቁ መሆናቸውን ለማረጋገጥ ጥረት አድርገዋል።
-
-
ይህ የመዳን ቀን ነው!መጠበቂያ ግንብ—1998 | ታኅሣሥ 15
-
-
በይሖዋ ማዳን ታመኑ
20. (ሀ) የጳውሎስ ልባዊ ፍላጎት ምን ነበር? በከንቱ የሚባክን ጊዜ ያልነበረውስ ለምንድን ነው? (ለ) ይህ የምንኖርበት ዘመን የመዳን ቀን መሆኑን ለይቶ የሚያሳውቀው ምንድን ነው?
20 ጳውሎስ በ55 እዘአ ገደማ ሁለተኛ ደብዳቤውን ለቆሮንቶስ ሰዎች ሲጽፍ የአይሁድ የነገሮች ሥርዓት ሊጠፋ የቀረው ጊዜ ከ15 ዓመታት የማይበልጥ ነበር። ሐዋርያው አይሁዳውያንና አሕዛብ በክርስቶስ አማካኝነት ከአምላክ ጋር እንዲታረቁ ልባዊ ፍላጎት ነበረው። ያ የመዳን ቀን ነበር፤ በከንቱ የሚባክን ጊዜ አልነበረም። እኛም ከ1914 ጀምሮ ተመሳሳይ በሆነ የነገሮች ሥርዓት ፍጻሜ ውስጥ እንገኛለን። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ በመካሄድ ላይ ያለው የመንግሥቱ ስብከት ሥራ ይህ ጊዜ የመዳን ቀን መሆኑን ለይቶ ያሳውቃል።
21. (ሀ) ለ1999 የተመረጠው የዓመት ጥቅስ የትኛው ነው? (ለ) በዚህ የመዳን ቀን ምን ማድረግ አለብን?
21 አምላክ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ያዘጋጀውን መዳን በሁሉም ብሔራት ውስጥ የሚገኙ ሕዝቦች መስማት ያስፈልጋቸዋል። ወደ ኋላ የምንልበት ጊዜ የለም። ጳውሎስ “እነሆ፣ የመዳን ቀን አሁን ነው” ሲል ጽፏል። እነዚህ በ2 ቆሮንቶስ 6:2 ላይ የሚገኙት ቃላት የይሖዋ ምሥክሮች የ1999 የዓመት ጥቅስ ይሆናሉ። ከኢየሩሳሌምና ከቤተ መቅደሷ ጥፋት ይበልጥ የከፋ ነገር ከፊታችን ስለሚጠብቀን ጥቅሱ ለጊዜያችን ምንኛ ተስማሚ ነው! በምድር ላይ ያለውን እያንዳንዱን ሰው የሚነካው የዚህ ጠቅላላ የነገሮች ሥርዓት ጥፋት ቀርቧል። እርምጃ መውሰድ ያለብን ነገ ሳይሆን ዛሬውኑ ነው። ማዳን የይሖዋ መሆኑን ካመንን፣ የምንወደውና የዘላለም ሕይወት ለማግኘት የምንፈልግ ከሆነ ይገባናል የማንለውን የአምላክ ደግነት ዓላማ አንስትም። ይሖዋን ለማክበር ባለን ልባዊ ፍላጎት “እነሆ፣ የመዳን ቀን አሁን ነው” ብለን ስንናገር ቃላችንም ሆነ ተግባራችን ከዚህ ጋር የሚስማማ መሆኑን እናረጋግጣለን።
-