-
ይሖዋ የሚሰጠውን ማጽናኛ ማካፈልመጠበቂያ ግንብ—1996 | ኅዳር 1
-
-
“ተስፋችንም ስለ እናንተ ጽኑ ነው፤ ሥቃያችንን እንደ ተካፈላችሁ እንዲሁም መጽናናታችንን ደግሞ እንድትካፈሉ እናውቃለንና።” —2 ቆሮንቶስ 1:7
-
-
ይሖዋ የሚሰጠውን ማጽናኛ ማካፈልመጠበቂያ ግንብ—1996 | ኅዳር 1
-
-
4. ለእውነት ፍላጎት ያሳዩ አዳዲስ ሰዎች ለሚደርስባቸው መከራ ምላሽ የሚሰጡት በምን የተለያዩ መንገዶች ሊሆን ይችላል?
4 የሚያሳዝነው ኢየሱስ አስቀድሞ እንደተናገረው አንዳንዶች ችግርና መከራው እንዲደናቀፉና ከክርስቲያን ጉባኤ ጋር ያላቸውን ግንኙነት እንዲያቋርጡ ያደርጋቸዋል። (ማቴዎስ 13:5, 6, 20, 21) ሌሎች ደግሞ እየተማሯቸው ባሉት አጽናኝ ተስፋዎች ላይ አእምሮአቸው እንዲያተኩር በማድረግ መከራውን ተቋቁመውታል። ከጊዜ በኋላም ሕይወታቸውን ለይሖዋ በመወሰን የልጁ የኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዛሙርት በመሆን ተጠምቀዋል። (ማቴዎስ 28:19, 20፤ ማርቆስ 8:34) እርግጥ አንድ ክርስቲያን ሲጠመቅ በእሱ ላይ የሚደርሰው መከራ ያቆማል ማለት አይደለም። ለምሳሌ ያህል ቀደም ሲል ብልሹ ሥነ ምግባር የነበረው ሰው ንጹሕ ሆኖ መኖር ከባድ ትግል ሊጠይቅበት ይችላል። ሌሎች ደግሞ ከማያምኑ የቤተሰብ አባላት የሚደርስባቸውን የማያቋርጥ ተቃውሞ መቋቋም አለባቸው። ራሳቸውን ለአምላክ ወስነው በታማኝነት የሚኖሩ ሁሉ የሚደርስባቸው መከራ ምንም ይሁን ምን ስለ አንድ ነገር እርግጠኞች መሆን ይችላሉ። በግለሰብ ደረጃ የአምላክን ማጽናኛና እርዳታ ያገኛሉ።
-