-
“በደስታና በመንፈስ ቅዱስ ተሞሉ”‘ስለ አምላክ መንግሥት በሚገባ መመሥከር’
-
-
10. ጳውሎስና በርናባስ ከጴርጌ ወደ ጵስድያዋ አንጾኪያ ያደረጉትን ጉዞ ግለጽ።
10 ጴርጌ ሲደርሱ ዮሐንስ ማርቆስ ትቷቸው ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሰ። ዮሐንስ ማርቆስ ድንገት የተመለሰበት ምክንያት አልተገለጸም። ጳውሎስና በርናባስ ጉዟቸውን ቀጠሉ፤ ከጴርጌ ተነስተው ወደ ጵስድያዋ አንጾኪያ ሄዱ፤ አንጾኪያ በገላትያ አውራጃ የምትገኝ ከተማ ነች። ጉዞው ቀላል አልነበረም፤ ምክንያቱም የጵስድያዋ አንጾኪያ የምትገኘው ከባሕር ጠለል በላይ 1,100 ሜትር ከፍታ ላይ ነው። ተራሮችን አቋርጠው የሚያልፉት አሳቻ መንገዶች ሽፍቶች የበዙባቸው ነበሩ። ይህ ሁሉ እንዳይበቃ ደግሞ በዚህ ወቅት ጳውሎስ የጤና እክል ሳያጋጥመው አልቀረም።h
-