-
4 | በአምላክ እርዳታ ጥላቻን ድል አድርግመጠበቂያ ግንብ (ለሕዝብ የሚሰራጭ)—2022 | ቁጥር 1
-
-
የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት፦
“የመንፈስ ፍሬ ፍቅር፣ ደስታ፣ ሰላም፣ ትዕግሥት፣ ደግነት፣ ጥሩነት፣ እምነት፣ ገርነት፣ ራስን መግዛት ነው።”—ገላትያ 5:22, 23
ምን ማለት ነው?
በአምላክ እርዳታ የጥላቻን ሰንሰለት መበጠስ እንችላለን። የአምላክ ቅዱስ መንፈስ በራሳችን ልናዳብር የማንችላቸውን ግሩም ባሕርያት እንድናፈራ ያስችለናል። ስለዚህ በራሳችን ኃይል ጥላቻን ለማሸነፍ ከመሞከር ይልቅ በአምላክ እርዳታ መታመናችን የተሻለ ነው። እንዲህ ካደረግን የሐዋርያው ጳውሎስ ዓይነት ስሜት ይኖረናል፤ ጳውሎስ “ኃይልን በሚሰጠኝ በእሱ አማካኝነት ለሁሉም ነገር የሚሆን ብርታት አለኝ” በማለት ጽፏል። (ፊልጵስዩስ 4:13) በእርግጥም “እኔን የሚረዳኝ . . . ይሖዋ ነው” ማለት እንችላለን።—መዝሙር 121:2
-