የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • መጽሐፍ ቅዱስን መማርህን እንድትቀጥል ምን ሊረዳህ ይችላል?
    ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
    • 4. ለመጽሐፍ ቅዱስ ጥናትህ ቅድሚያ ስጥ

      አንዳንዴ ጊዜያችን በጣም ከመጣበቡ የተነሳ መጽሐፍ ቅዱስን ለመማር በቂ ጊዜ እንደሌለን ይሰማን ይሆናል። ታዲያ ምን ሊረዳን ይችላል? ፊልጵስዩስ 1:10⁠ን አንብቡ፤ ከዚያም በሚከተሉት ጥያቄዎች ላይ ተወያዩ፦

      • በሕይወታችን ውስጥ ‘ይበልጥ አስፈላጊ ከሆኑት ነገሮች’ አንዳንዶቹ የትኞቹ ይመስሉሃል?

      • ለመጽሐፍ ቅዱስ ጥናትህ ቅድሚያ ለመስጠት ምን ማድረግ ይኖርብሃል?

      ሀ. አንድ ባልዲ በድንጋይና በአሸዋ ተሞልቶ የሚያሳዩ ሥዕሎች፦ 1. የተቆለለ አሸዋና ድንጋይ 2. ከግማሽ በላይ በአሸዋ የተሞላ ባልዲ 3. ከትላልቆቹ ድንጋዮች መካከል የተወሰኑት አሸዋው ላይ ተቀምጠዋል፤ የቀሩት ደግሞ መሬት ላይ ወድቀዋል ለ. 1. ቀደም ሲል የታየው የተቆለለ አሸዋና ድንጋይ 2. ያው ባልዲ በድንጋይ ተሞልቶ 3. አሸዋው ባልዲ ውስጥ ከድንጋዮቹ በተረፈው ቦታ ላይ ተሞልቷል፤ አብዛኛው አሸዋ ባልዲው ውስጥ ገብቶ የቀረው ጥቂት አሸዋ መሬት ላይ ተቀምጧል
      1. ሀ. ባልዲው ውስጥ መጀመሪያ ላይ አሸዋ ከጨመርክ በኋላ ድንጋዮቹን ለመጨመር ብትሞክር ለሁሉም ድንጋዮች የሚሆን በቂ ቦታ አታገኝም

      2. ለ. አስቀድመህ ድንጋዮቹን ካስገባህ ግን አብዛኛውን አሸዋ ለማስገባት የሚያስችል ቦታ ታገኛለህ። በተመሳሳይም በሕይወት ውስጥ ‘ይበልጥ አስፈላጊ ለሆኑት ነገሮች’ ቅድሚያ ከሰጠህ ለሌሎች ነገሮችም የሚሆን ጊዜ ታገኛለህ

      መጽሐፍ ቅዱስን መማራችን መንፈሳዊ ፍላጎታችንን ማለትም አምላክን የማወቅና እሱን የማምለክ ፍላጎታችንን ለማሟላት ያስችለናል። ማቴዎስ 5:3⁠ን አንብቡ፤ ከዚያም በሚከተለው ጥያቄ ላይ ተወያዩ፦

      • ለመጽሐፍ ቅዱስ ጥናታችን ቅድሚያ መስጠታችን ምን ጥቅም ያስገኝልናል?

  • የመዝናኛ ምርጫህ ይሖዋን የሚያስደስት ይሁን
    ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
    • 4. ጊዜህን በጥበብ ተጠቀም

      ቪዲዮውን ተመልከቱ፤ ከዚያም በሚከተለው ጥያቄ ላይ ተወያዩ፦

      ቪዲዮ፦ ጊዜያችሁን የሚይዝባችሁ ምንድን ነው? (2:45)

      • በቪዲዮው ላይ የታየው ወንድም መጥፎ ነገር ባይመለከትም ትርፍ ጊዜውን የሚጠቀምበት መንገድ ምን ተጽዕኖ አሳድሮበታል?

      ፊልጵስዩስ 1:10⁠ን አንብቡ፤ ከዚያም በሚከተለው ጥያቄ ላይ ተወያዩ፦

      • ይህ ጥቅስ በመዝናኛ ምን ያህል ጊዜ ማሳለፍ እንዳለብን ለመወሰን የሚረዳን እንዴት ነው?

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ