የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ፆታ ግንኙነት ምን ይላል?
    ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
    • 4. ፈታኝ ሁኔታዎችን መቋቋም ትችላለህ

      የፆታ ብልግና እንድንፈጽም የሚደረግብንን ጫና መቋቋም ከባድ እንዲሆንብን የሚያደርገው ምን ሊሆን ይችላል? ቪዲዮውን ተመልከቱ፤ ከዚያም በሚከተለው ጥያቄ ላይ ተወያዩ፦

      ቪዲዮ፦ መጽሐፍ ቅዱስን ማንበብ ፈተናን ለመቋቋም ይረዳል (3:02)

      • በቪዲዮው ላይ የታየው ወንድም፣ የሚያስባቸውና የሚያደርጋቸው አንዳንድ ነገሮች ለባለቤቱ ያለውን ታማኝነት እንዲያጓድል ሊያደርጉት እንደሚችሉ ሲገነዘብ ምን አደረገ?

      ታማኝ ክርስቲያኖችም እንኳ አስተሳሰባቸው ምንጊዜም ንጹሕ እንዲሆን ለማድረግ መታገል ሊያስፈልጋቸው ይችላል። የብልግና ሐሳቦችን እንዳታውጠነጥን ምን ይረዳሃል? ፊልጵስዩስ 4:8⁠ን አንብቡ፤ ከዚያም በሚከተሉት ጥያቄዎች ላይ ተወያዩ፦

      • ስለ ምን ነገሮች ማሰብ ይኖርብናል?

      • መጽሐፍ ቅዱስን ማንበባችንና በይሖዋ አገልግሎት በትጋት መካፈላችን ኃጢአት ለመፈጸም ስንፈተን የሚረዳን እንዴት ነው?

  • በንግግርህ ይሖዋን ማስደሰት የምትችለው እንዴት ነው?
    ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
    • 3. ሌሎችን በሚያበረታታ መንገድ ለመናገር ምን ይረዳናል?

      አብዛኛውን ጊዜ የምንናገረው ነገር በልባችን ውስጥ ያለውን ወይም የምናስበውን ነገር ያንጸባርቃል። (ሉቃስ 6:45) በመሆኑም ጥሩ በሆኑ ነገሮች ላይ ማለትም ጽድቅ፣ ንጹሕና ተወዳጅ በሆኑ እንዲሁም በመልካም በሚነሱ ነገሮች ላይ ለማተኮር ራሳችንን ማሠልጠን ያስፈልገናል። (ፊልጵስዩስ 4:8) በእነዚህ ነገሮች ላይ ለማተኮር በመዝናኛና በጓደኛ ምርጫችን ረገድ ጠንቃቆች መሆን አለብን። (ምሳሌ 13:20) በተጨማሪም ከመናገራችን በፊት ማሰባችን ይረዳናል። የምትናገረው ነገር በሌሎች ላይ ምን ስሜት እንደሚያሳድር አስብ። መጽሐፍ ቅዱስ “ሳይታሰብበት የሚነገር ቃል እንደ ሰይፍ ይወጋል፤ የጥበበኞች ምላስ ግን ፈውስ ነው” ይላል።—ምሳሌ 12:18

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ