የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ምሥራቹን ለሌሎች መናገር የምትችለው እንዴት ነው?
    ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
    • 1. የተማርከውን ነገር ለምታውቃቸው ሰዎች መናገር የምትችለው እንዴት ነው?

      የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት “ስላየነውና ስለሰማነው ነገር ከመናገር ወደኋላ ማለት አንችልም” ብለው ነበር። (የሐዋርያት ሥራ 4:20) ለተማሩት እውነት ከፍተኛ አድናቆት ስለነበራቸው ይህን እውነት ላገኙት ሰው ሁሉ መናገር ፈልገው ነበር። አንተስ እንዲህ ይሰማሃል? ከሆነ የተማርከውን ነገር ለቤተሰቦችህና ለጓደኞችህ በአክብሮት መናገር የምትችልባቸውን አጋጣሚዎች ፈልግ።—ቆላስይስ 4:6⁠ን አንብብ።

      ምሥራቹን መናገር መጀመር የምትችልባቸው አንዳንድ መንገዶች

      • ከቤተሰብህ ጋር ስትጨዋወት ‘በዚህ ሳምንት የተማርኩትን ደስ የሚል ነገር ልንገራችሁ’ በማለት አንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ሐሳብ ንገራቸው።

      • ለታመመ ወይም በጭንቀት ለተዋጠ ጓደኛህ አንድ የሚያበረታታ ጥቅስ አንብብለት።

      • የሥራ ባልደረቦችህ ‘ሳምንቱ እንዴት ነበር?’ ብለው ሲጠይቁህ በመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ፕሮግራምህ ላይ ወይም በጉባኤ ስብሰባ ላይ የተማርከውን ነገር ንገራቸው።

      • ለጓደኞችህ jw.org ድረ ገጽን አሳያቸው።

      • ሌሎች በመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ፕሮግራምህ ላይ እንዲገኙ ጋብዝ፤ ወይም jw.org ላይ የሚገኘውን ቅጽ ተጠቅመው መጽሐፍ ቅዱስን ለመማር መጠየቅ የሚችሉት እንዴት እንደሆነ አሳያቸው።

  • ምሥራቹን ለሌሎች መናገር የምትችለው እንዴት ነው?
    ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
    • 4. አክብሮት አሳይ

      ለሌሎች ምሥራቹን ስትናገር የምትናገረው ነገር ብቻ ሳይሆን የምትናገርበት መንገድም ሊያሳስብህ ይገባል። ሁለተኛ ጢሞቴዎስ 2:24⁠ን እና 1 ጴጥሮስ 3:15⁠ን አንብቡ፤ ከዚያም በሚከተሉት ጥያቄዎች ላይ ተወያዩ፦

      • ከሌሎች ጋር ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ስትነጋገር በእነዚህ ጥቅሶች ላይ ያለውን ምክር ተግባራዊ ማድረግ የምትችለው እንዴት ነው?

      • አንዳንድ የቤተሰብህ አባላት ወይም ጓደኞችህ በምትናገረው ነገር ላይስማሙ ይችላሉ። በዚህ ጊዜ ምን ልታደርግ ትችላለህ? ምን ልታደርግስ አይገባም?

      • ሰዎች የምትናገረውን ነገር እንዲቀበሉ ከመጫን ይልቅ በዘዴ አንዳንድ ጥያቄዎችን መጠየቅ የተሻለ የሚሆነው ለምንድን ነው?

      አንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ተማሪ ከመጽሐፍ ቅዱስ ላይ ያገኘውን ሐሳብ ለዘመዱ ሲናገር
አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ