-
ምሥራቹን ለሌሎች መናገር የምትችለው እንዴት ነው?ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
-
-
1. የተማርከውን ነገር ለምታውቃቸው ሰዎች መናገር የምትችለው እንዴት ነው?
የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት “ስላየነውና ስለሰማነው ነገር ከመናገር ወደኋላ ማለት አንችልም” ብለው ነበር። (የሐዋርያት ሥራ 4:20) ለተማሩት እውነት ከፍተኛ አድናቆት ስለነበራቸው ይህን እውነት ላገኙት ሰው ሁሉ መናገር ፈልገው ነበር። አንተስ እንዲህ ይሰማሃል? ከሆነ የተማርከውን ነገር ለቤተሰቦችህና ለጓደኞችህ በአክብሮት መናገር የምትችልባቸውን አጋጣሚዎች ፈልግ።—ቆላስይስ 4:6ን አንብብ።
ምሥራቹን መናገር መጀመር የምትችልባቸው አንዳንድ መንገዶች
ከቤተሰብህ ጋር ስትጨዋወት ‘በዚህ ሳምንት የተማርኩትን ደስ የሚል ነገር ልንገራችሁ’ በማለት አንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ሐሳብ ንገራቸው።
ለታመመ ወይም በጭንቀት ለተዋጠ ጓደኛህ አንድ የሚያበረታታ ጥቅስ አንብብለት።
የሥራ ባልደረቦችህ ‘ሳምንቱ እንዴት ነበር?’ ብለው ሲጠይቁህ በመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ፕሮግራምህ ላይ ወይም በጉባኤ ስብሰባ ላይ የተማርከውን ነገር ንገራቸው።
ለጓደኞችህ jw.org ድረ ገጽን አሳያቸው።
ሌሎች በመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ፕሮግራምህ ላይ እንዲገኙ ጋብዝ፤ ወይም jw.org ላይ የሚገኘውን ቅጽ ተጠቅመው መጽሐፍ ቅዱስን ለመማር መጠየቅ የሚችሉት እንዴት እንደሆነ አሳያቸው።
-
-
ምሥራቹን ለሌሎች መናገር የምትችለው እንዴት ነው?ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
-
-
4. አክብሮት አሳይ
ለሌሎች ምሥራቹን ስትናገር የምትናገረው ነገር ብቻ ሳይሆን የምትናገርበት መንገድም ሊያሳስብህ ይገባል። ሁለተኛ ጢሞቴዎስ 2:24ን እና 1 ጴጥሮስ 3:15ን አንብቡ፤ ከዚያም በሚከተሉት ጥያቄዎች ላይ ተወያዩ፦
ከሌሎች ጋር ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ስትነጋገር በእነዚህ ጥቅሶች ላይ ያለውን ምክር ተግባራዊ ማድረግ የምትችለው እንዴት ነው?
አንዳንድ የቤተሰብህ አባላት ወይም ጓደኞችህ በምትናገረው ነገር ላይስማሙ ይችላሉ። በዚህ ጊዜ ምን ልታደርግ ትችላለህ? ምን ልታደርግስ አይገባም?
ሰዎች የምትናገረውን ነገር እንዲቀበሉ ከመጫን ይልቅ በዘዴ አንዳንድ ጥያቄዎችን መጠየቅ የተሻለ የሚሆነው ለምንድን ነው?
-