-
መንጋውን በእረኝነት የሚጠብቁ የበላይ ተመልካቾችየይሖዋን ፈቃድ ለማድረግ የተደራጀ ሕዝብ
-
-
5 ሐዋርያው ጳውሎስ ለጢሞቴዎስ በጻፈው የመጀመሪያ ደብዳቤውና ለቲቶ በላከው ደብዳቤ ላይ የበላይ ተመልካቾች የሚጠበቁባቸውን መሠረታዊ የሆኑ ቅዱስ ጽሑፋዊ ብቃቶች ዘርዝሯል። አንደኛ ጢሞቴዎስ 3:1-7 እንዲህ ይላል፦ “የበላይ ተመልካች ለመሆን የሚጣጣር ሰው መልካም ሥራን ይመኛል። ስለዚህ የበላይ ተመልካች የማይነቀፍ፣ የአንዲት ሚስት ባል፣ በልማዶቹ ልከኛ የሆነ፣ ጤናማ አስተሳሰብ ያለው፣ ሥርዓታማ፣ እንግዳ ተቀባይ፣ የማስተማር ብቃት ያለው፣ የማይሰክር፣ ኃይለኛ ያልሆነ፣ ይልቁንም ምክንያታዊ የሆነ፣ የማይጣላ፣ ገንዘብ ወዳድ ያልሆነ፣ ታዛዥና ቁም ነገረኛ የሆኑ ልጆች ያሉትና የራሱን ቤተሰብ በተገቢው ሁኔታ የሚያስተዳድር ሊሆን ይገባዋል፤ (ደግሞስ አንድ ሰው የራሱን ቤተሰብ እንዴት እንደሚያስተዳድር ካላወቀ የአምላክን ጉባኤ እንዴት ሊንከባከብ ይችላል?) በትዕቢት ተነፍቶ ዲያብሎስ የተፈረደበት ዓይነት ፍርድ እንዳይፈረድበት አዲስ ክርስቲያን አይሁን። ከዚህም በተጨማሪ እንዳይነቀፍና በዲያብሎስ ወጥመድ ውስጥ እንዳይወድቅ በውጭ ባሉት ሰዎች ዘንድ በመልካም የተመሠከረለት ሊሆን ይገባል።”
-
-
መንጋውን በእረኝነት የሚጠብቁ የበላይ ተመልካቾችየይሖዋን ፈቃድ ለማድረግ የተደራጀ ሕዝብ
-
-
8 የበላይ ተመልካች ሆነው የሚሾሙ ወንዶች፣ ገና ልጆች ወይም አዲስ ክርስቲያኖች መሆን የለባቸውም። ከዚህ ይልቅ በክርስቲያናዊ አኗኗር ተሞክሮ ያካበቱ፣ ሰፊ የመጽሐፍ ቅዱስ እውቀት ያላቸው፣ ቅዱሳን መጻሕፍትን በጥልቀት የሚረዱ እንዲሁም ለጉባኤው ልባዊ ፍቅር ያላቸው ግለሰቦች ናቸው። መጥፎ ድርጊት የሚፈጽሙ ሰዎችን በድፍረት ከመናገርና ከማረም ወደኋላ አይሉም፤ ይህም ራስ ወዳድ የሆኑ ሰዎች መንጋውን መጠቀሚያ እንዳያደርጉት ለመከላከል ያስችላል። (ኢሳ. 32:2) የበላይ ተመልካቾቹ በመንፈሳዊ የጎለመሱና ለአምላክ መንጋ ከልብ የሚያስቡ ሰዎች መሆናቸውን በጉባኤው ውስጥ ያሉ ሁሉ ይቀበላሉ።
-