የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ይሖዋ ይደግፍሃል
    መጠበቂያ ግንብ—2015 | ታኅሣሥ 15
    • 13. ከጤና ጋር በተያያዘ የሚሰጡ አስተያየቶችን በተመለከተ ምን ዓይነት ሚዛናዊ አመለካከት መያዝ ተገቢ ነው?

      13 በዛሬው ጊዜ አንድ ክርስቲያን ‘በመፈወስ ስጦታ’ ተጠቅሞ ከሕመማችን ሊያድነን አይችልም። ይሁንና አንዳንድ ወንድሞች ምክር ባንጠይቃቸውም እንኳ በአሳቢነት ተነሳስተው ከጤና ጋር የተያያዙ አስተያየቶችን ይሰጣሉ። በእርግጥ አንዳንዶች የሚሰጡት ሐሳብ ጠቃሚ ሊሆን ይችላል። ጢሞቴዎስ በአካባቢው ያለው ውኃ በመበከሉ የተነሳ ሳይሆን አይቀርም፣ ሆዱን ባመመው ጊዜ ጳውሎስ እንዲህ ዓይነት ምክር ሰጥቶታል።a (1 ጢሞቴዎስ 5:23⁠ን አንብብ።) ይህ ግን የእምነት ባልንጀራችን፣ አንዳንድ ዕፀዋትን ወይም መድኃኒቶችን እንዲወስድ አሊያም አንድን የአመጋገብ ሥርዓት እንዲከተል ለማሳመን ከመሞከር በጣም የተለየ ነው፤ ምናልባትም ይህ ዓይነቱ ሕክምና ውጤታማ ላይሆን እንዲያውም አንዳንድ ጊዜ ጉዳት ሊያስከትል ይችላል። አንዳንድ ጊዜ የጤና ምክር የሚሰጡ ሰዎች ‘አንድ ዘመዴ እንዲህ ዓይነት ሕመም ነበረበት፤ . . . ሲወስድ ግን ተሻለው’ እንደሚለው ዓይነት ሐሳብ ሲሰነዝሩ ይሰማል። ምክሩ የተሰጠው በአሳቢነት ሊሆን ይችላል፤ ያም ቢሆን በሰፊው የሚሠራበት መድኃኒትም ሆነ የሕክምና ዓይነት እንኳ ጉዳት ሊያስከትል እንደሚችል ማስታወስ ይኖርብናል።—ምሳሌ 27:12⁠ን አንብብ።

  • ይሖዋ ይደግፍሃል
    መጠበቂያ ግንብ—2015 | ታኅሣሥ 15
    • a ዚ ኦሪጅንስ ኤንድ ኤንሸንት ሂስትሪ ኦቭ ዋይን የተባለው መጽሐፍ እንዲህ ይላል፦ “የታይፎይድ በሽታ አምጪ ተሕዋስያንን እና ሌሎች አደገኛ የሆኑ በዓይን የማይታዩ ሕይወት ያላቸው ነገሮችን የወይን ጠጅ ወዲያውኑ እንደሚገድላቸው በቤተ ሙከራ ማረጋገጥ ተችሏል።”

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ