የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ገንዘብ የክፋት ሁሉ ሥር ነው?
    የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው
    • አንድ ሰው ገንዘብ ለማፈስ ሲሞክር።

      ገንዘብ የክፋት ሁሉ ሥር ነው?

      መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል?

      አይደለም። መጽሐፍ ቅዱስ፣ ገንዘብ መጥፎ ነገር እንደሆነ አይገልጽም፤ ገንዘብ የክፉ ነገሮች ሁሉ መንስኤ እንደሆነም አይናገርም። ከመጽሐፍ ቅዱስ እንደተወሰደ የሚነገርለት “ገንዘብ የክፋት ሁሉ ሥር ነው” የሚለው የተለመደ አባባል የጥቅሱን የተሟላ ሐሳብ ያልያዘና የተሳሳተ መልእክት የሚያስተላልፍ ነው። ትክክለኛው የጥቅሱ ሐሳብ “ገንዘብን መውደድ የክፋት ሁሉ ሥር ነው”a የሚል ነው።—1 ጢሞቴዎስ 6:10 የ1954 ትርጉም፤ ጎላ አድርገን የጻፍነው እኛ ነን።

  • ገንዘብ የክፋት ሁሉ ሥር ነው?
    የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው
    • 1 ጢሞቴዎስ 6:10፦ “የገንዘብ ፍቅር የብዙ ዓይነት ጎጂ ነገሮች ሥር ነውና፤ አንዳንዶች በዚህ ፍቅር ተሸንፈው ከእምነት ጎዳና ስተው ወጥተዋል፤ እንዲሁም ሁለንተናቸውን በብዙ ሥቃይ ወግተዋል።”

      ትርጉሙ፦ ገንዘብ በራሱ መጥፎ ነገር አይደለም። ሆኖም ገንዘብን የሚወዱ ይኸውም በሕይወታቸው ውስጥ ትልቁን ቦታ ለገንዘብ የሚሰጡ ሰዎች በራሳቸው ላይ ችግሮች ያመጣሉ፤ ከእነዚህ ችግሮች መካከል የቤተሰብ መፍረስ እንዲሁም ከልክ በላይ በመሥራት የሚመጣ የጤና መቃወስ ይገኙበታል።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ