-
መንጋውን በእረኝነት የሚጠብቁ የበላይ ተመልካቾችየይሖዋን ፈቃድ ለማድረግ የተደራጀ ሕዝብ
-
-
5 ሐዋርያው ጳውሎስ ለጢሞቴዎስ በጻፈው የመጀመሪያ ደብዳቤውና ለቲቶ በላከው ደብዳቤ ላይ የበላይ ተመልካቾች የሚጠበቁባቸውን መሠረታዊ የሆኑ ቅዱስ ጽሑፋዊ ብቃቶች ዘርዝሯል። አንደኛ ጢሞቴዎስ 3:1-7 እንዲህ ይላል፦ “የበላይ ተመልካች ለመሆን የሚጣጣር ሰው መልካም ሥራን ይመኛል። ስለዚህ የበላይ ተመልካች የማይነቀፍ፣ የአንዲት ሚስት ባል፣ በልማዶቹ ልከኛ የሆነ፣ ጤናማ አስተሳሰብ ያለው፣ ሥርዓታማ፣ እንግዳ ተቀባይ፣ የማስተማር ብቃት ያለው፣ የማይሰክር፣ ኃይለኛ ያልሆነ፣ ይልቁንም ምክንያታዊ የሆነ፣ የማይጣላ፣ ገንዘብ ወዳድ ያልሆነ፣ ታዛዥና ቁም ነገረኛ የሆኑ ልጆች ያሉትና የራሱን ቤተሰብ በተገቢው ሁኔታ የሚያስተዳድር ሊሆን ይገባዋል፤ (ደግሞስ አንድ ሰው የራሱን ቤተሰብ እንዴት እንደሚያስተዳድር ካላወቀ የአምላክን ጉባኤ እንዴት ሊንከባከብ ይችላል?) በትዕቢት ተነፍቶ ዲያብሎስ የተፈረደበት ዓይነት ፍርድ እንዳይፈረድበት አዲስ ክርስቲያን አይሁን። ከዚህም በተጨማሪ እንዳይነቀፍና በዲያብሎስ ወጥመድ ውስጥ እንዳይወድቅ በውጭ ባሉት ሰዎች ዘንድ በመልካም የተመሠከረለት ሊሆን ይገባል።”
-
-
መንጋውን በእረኝነት የሚጠብቁ የበላይ ተመልካቾችየይሖዋን ፈቃድ ለማድረግ የተደራጀ ሕዝብ
-
-
7 ከበላይ ተመልካቾች የሚጠበቁት ቅዱስ ጽሑፋዊ ብቃቶች መጀመሪያ ላይ በጣም ከባድ ቢመስሉም ክርስቲያን ወንዶች የበላይ ተመልካች ለመሆን ከመጣጣር መሸሽ አይኖርባቸውም። ከበላይ ተመልካቾች የሚጠበቁትን ክርስቲያናዊ ባሕርያት ሲያንጸባርቁ በጉባኤው ውስጥ ያሉ ሌሎች ክርስቲያኖች የእነሱን ምሳሌ ለመከተል ይነሳሳሉ። ጳውሎስ እነዚህ ሰዎች ‘ስጦታ ሆነው የተሰጡት’ ለምን እንደሆነ ሲጽፍ እንዲህ ብሏል፦ “ይህን ያደረገው ቅዱሳንን እንዲያስተካክሉ፣ ሌሎችን እንዲያገለግሉና የክርስቶስን አካል እንዲገነቡ ነው፤ ይህም ሁላችንም በእምነትና ስለ አምላክ ልጅ ትክክለኛ እውቀት በመቅሰም ወደሚገኘው አንድነት እንዲሁም ሙሉ ሰው ወደ መሆን ይኸውም እንደ ክርስቶስ የተሟላ የጉልምስና ደረጃ ላይ እስክንደርስ ድረስ ነው።”—ኤፌ. 4:8, 12, 13
-