-
መንጋውን በእረኝነት የሚጠብቁ የበላይ ተመልካቾችየይሖዋን ፈቃድ ለማድረግ የተደራጀ ሕዝብ
-
-
9 የበላይ ተመልካች ሆነው የሚሾሙ ወንዶች ሕይወታቸውን በጥበብ እንደሚመሩ መታየት አለበት። አንድ የበላይ ተመልካች ያገባ ከሆነ ትዳርን በተመለከተ የወጣውን ክርስቲያናዊ መሥፈርት በጥብቅ ይከተላል፤ ይህም ማለት የአንዲት ሚስት ባል ሊሆን ይገባል እንዲሁም የራሱን ቤተሰብ በተገቢው ሁኔታ ማስተዳደር ይኖርበታል። የበላይ ተመልካቹ ታዛዥና ቁም ነገረኛ የሆኑ እንዲሁም በስድነት ወይም በዓመፀኝነት የማይከሰሱ አማኝ የሆኑ ልጆች ካሉት በጉባኤው ውስጥ ያሉት ወንድሞችና እህቶች የቤተሰብ ሕይወትንና ክርስቲያናዊ አኗኗርን በተመለከተ ምክርና ማበረታቻ እንደሚያገኙ እርግጠኛ ሆነው ወደ እሱ ሊመጡ ይችላሉ። ከዚህም በተጨማሪ አንድ የበላይ ተመልካች የማይነቀፍ እና ከክስ ነፃ እንዲሁም በውጭ ባሉት ሰዎች ዘንድ ጭምር በመልካም የተመሠከረለት መሆን አለበት። የጉባኤውን ስም የሚያጎድፍ ተገቢ ያልሆነ ምግባር ፈጽሟል የሚል መሠረት ያለው ክስ የሚሰነዘርበት ሊሆን አይገባም። ከባድ ስህተት በመፈጸሙ በቅርቡ ተግሣጽ የተሰጠው መሆን የለበትም። በጉባኤው ውስጥ ያሉ ሌሎች አስፋፊዎች የእሱን መልካም አርዓያ ለመኮረጅ ሊነሳሱ እንዲሁም ለመንፈሳዊ ሕይወታቸው አስፈላጊውን እንክብካቤ ሊያደርግላቸው እንደሚችል ሊተማመኑበት ይገባል።—1 ቆሮ. 11:1፤ 16:15, 16
10 እንዲህ ያሉት ብቃት ያላቸው ወንዶች፣ “ጥበበኛና አስተዋይ የሆኑ እንዲሁም ተሞክሮ ያካበቱ” ተብለው ከተገለጹት የእስራኤል ሽማግሌዎች ጋር የሚመሳሰል ሚና በክርስቲያን ጉባኤ ውስጥ ሊጫወቱ ይችላሉ። (ዘዳ. 1:13) ክርስቲያን ሽማግሌዎች ከኃጢአት ነፃ አይደሉም፤ ያም ሆኖ አምላክ ካወጣቸው መሠረታዊ ሥርዓቶች ጋር የሚስማማ ሕይወት በመምራት በጉባኤውም ሆነ በኅብረተሰቡ ዘንድ ቅንና አምላክን የሚፈሩ ሰዎች መሆናቸውን አስመሥክረዋል። ነቀፋ የሌለባቸው መሆናቸው በጉባኤው ፊት በነፃነት እንዲናገሩ ያስችላቸዋል።—ሮም 3:23
-
-
መንጋውን በእረኝነት የሚጠብቁ የበላይ ተመልካቾችየይሖዋን ፈቃድ ለማድረግ የተደራጀ ሕዝብ
-
-
11 የበላይ ተመልካች ሆነው ለመሾም የሚበቁ ወንዶች ከሌሎች ጋር ባላቸው ግንኙነትም ሆነ በልማዳቸው ልከኛ ናቸው። ጽንፈኞች አይደሉም። ከዚህ ይልቅ በአኗኗራቸው ሚዛናዊና ራሳቸውን የሚገዙ ናቸው። በመብል፣ በመጠጥ፣ በመዝናኛ፣ በትርፍ ጊዜ በሚሠሩ ነገሮችና እነዚህን በመሳሰሉ ሁኔታዎች ልከኛ መሆናቸውን ያሳያሉ። ሰካራም ተብለው እንዳይከሰሱ በአልኮል መጠጥ ረገድ ልከኛ ይሆናሉ። የሚያሰክር መጠጥ ወስዶ ስሜቱ የደነዘዘበት ሰው ራሱን መግዛት ያቅተዋል፤ ስለዚህ ለጉባኤው መንፈሳዊ ጉዳዮች ተገቢውን ትኩረት መስጠት አይችልም።
12 አንድ ሰው የጉባኤውን ጉዳዮች ለመምራት በቅድሚያ ሥርዓታማ መሆኑ መታየት ይኖርበታል። ውጪያዊ ቁመናው፣ ቤቱን የሚይዝበት መንገድና የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴው ጥሩ ልማድ እንዳለው የሚያሳይ መሆን ይኖርበታል። እንደዚህ ያለው ሰው ዛሬ ነገ እያለ ሥራ አያጓትትም፤ ምን እንደሚያስፈልግ በማስተዋል አስፈላጊውን ዕቅድ ያወጣል። ደግሞም አምላክ ያወጣቸውን መሠረታዊ ሥርዓቶች በጥብቅ ይከተላል።
-
-
መንጋውን በእረኝነት የሚጠብቁ የበላይ ተመልካቾችየይሖዋን ፈቃድ ለማድረግ የተደራጀ ሕዝብ
-
-
14 ከዚህም ሌላ በጉባኤው ውስጥ የበላይ ተመልካች ሆኖ ለማገልገል የሚሾም ሰው ጤናማ አስተሳሰብ ያለው መሆን ይኖርበታል። ይህም ማለት ለመፍረድ የማይቸኩል አስተዋይ ሰው ይሆናል ማለት ነው። ይሖዋ ያወጣቸው መሠረታዊ ሥርዓቶች ምን እንደሆኑና እንዴት በሥራ ላይ እንደሚውሉ ጥሩ ግንዛቤ አለው። ጤናማ አስተሳሰብ ያለው ሰው ምክርና መመሪያ ሲሰጠው በትሕትና ይቀበላል። እንዲሁም ግብዝ አይደለም።
-
-
መንጋውን በእረኝነት የሚጠብቁ የበላይ ተመልካቾችየይሖዋን ፈቃድ ለማድረግ የተደራጀ ሕዝብ
-
-
15 ጳውሎስ አንድ የበላይ ተመልካች ጥሩ የሆነውን ነገር የሚወድ መሆን እንዳለበት ቲቶን አሳስቦታል። ጻድቅ እና ታማኝ መሆን አለበት። ከሌሎች ጋር ባለው ግንኙነት እንዲሁም ትክክልና ጥሩ ለሆነው ነገር በሚወስደው ጽኑ አቋም እነዚህን ባሕርያት ያንጸባርቃል። ምንጊዜም ለይሖዋ ያደረ ከመሆኑም ሌላ ከጽድቅ መሠረታዊ ሥርዓቶች ጎን በታማኝነት ይቆማል። ሚስጥር ጠባቂም ነው። በተጨማሪም ራሱንም ሆነ ንብረቱን በፈቃደኝነት ለሌሎች ጥቅም በመስጠት ከልቡ እንግዳ ተቀባይ መሆኑን ያሳያል።—ሥራ 20:33-35
16 አንድ የበላይ ተመልካች ኃላፊነቱን ውጤታማ በሆነ መንገድ እንዲያከናውን ከተፈለገ የማስተማር ብቃት ያለው መሆን ይኖርበታል። ጳውሎስ ለቲቶ በጻፈው ደብዳቤ ላይ እንደገለጸው አንድ የበላይ ተመልካች “ትክክለኛ በሆነው ትምህርት ማበረታታትም ሆነ ይህን ትምህርት የሚቃወሙትን መውቀስ ይችል ዘንድ የማስተማር ጥበቡን ሲጠቀም የታመነውን ቃል በጥብቅ የሚከተል ሊሆን ይገባል።” (ቲቶ 1:9) የበላይ ተመልካቹ ማብራሪያ መስጠት፣ ማስረጃ ማቅረብ፣ ተቃውሞ ሲሰነዘር አጥጋቢ መልስ መስጠት እንዲሁም ሌሎችን በሚያሳምንና እምነታቸውን በሚያጠነክር መንገድ ጥቅሶችን መጠቀም መቻል አለበት። አመቺ በሆነ ጊዜም ይሁን በአስቸጋሪ ጊዜ እንዲህ ዓይነቱን የማስተማር ችሎታ መጠቀም ይኖርበታል። (2 ጢሞ. 4:2) የተሳሳቱ ሰዎችን በገርነት ለመውቀስ ወይም ተጠራጣሪ የሆኑትን ለማሳመንና በእምነት ላይ የተመሠረቱ ጠቃሚ ሥራዎች እንዲያከናውኑ ለማነሳሳት የሚያስችል ትዕግሥት አለው። አንድ የበላይ ተመልካች በስብሰባዎች ላይ ወይም በግለሰብ ደረጃ ሰዎችን ጥሩ አድርጎ የማስተማር ችሎታ ካለው ወሳኝ የሆነውን የማስተማር ብቃት አሟልቷል ሊባል ይችላል።
-