የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ማርቆስ—‘ለአገልግሎት የሚጠቅም ሰው’
    መጠበቂያ ግንብ—2010 | መጋቢት 15
    • ጳውሎስ በ65 ዓ.ም. ገደማ ለሁለተኛ ጊዜ ሮም ውስጥ በታሰረበት ወቅት ጢሞቴዎስ ከኤፌሶን ወደ ሮም እንዲመጣ ደብዳቤ ጽፎለት ነበር፤ በዚያ ደብዳቤ ላይ ‘ማርቆስን ከአንተ ጋር ይዘኸው ና’ ብሎት ነበር። (2 ጢሞ. 4:11) ከዚህ ማየት እንደሚቻለው ማርቆስ በዚያ ጊዜ ኤፌሶን ነበር። የጳውሎስን ጥሪ ተቀብሎ ከጢሞቴዎስ ጋር ወደ ሮም ተመልሶ እንደሄደ ጥርጥር የለውም። በዚያን ወቅት ጉዞ ማድረግ ቀላል አልነበረም፤ ሆኖም ማርቆስ በፈቃደኝነት ወደተለያዩ ቦታዎች ተጉዟል።

  • ማርቆስ—‘ለአገልግሎት የሚጠቅም ሰው’
    መጠበቂያ ግንብ—2010 | መጋቢት 15
    • ‘ለአገልግሎት ይጠቅመኛል’

      ማርቆስ ሮም ሳለ ወንጌል በመጻፍ ብቻ አልተወሰነም። ጳውሎስ ለጢሞቴዎስ ‘ማርቆስን ከአንተ ጋር ይዘኸው ና’ ያለውን አስታውስ። ጳውሎስ ይህን ያለው ለምን ነበር? ‘ለአገልግሎት ስለሚጠቅመው’ ነበር።—2 ጢሞ. 4:11

      ወደ መጨረሻ ከተጻፉት ቅዱሳን መጻሕፍት መካከል በሆነው በዚህ ደብዳቤ ላይ ማርቆስ መጠቀሱ ስለ እሱ ብዙ ነገሮችን እንድናውቅ ያስችለናል። ማርቆስ ባሳለፈው ቲኦክራሲያዊ ታሪክ ላይ በየትኛውም ቦታ ላይ እንደ ሐዋርያ፣ መሪ ወይም ነቢይ ተደርጎ አልተጠቀሰም። ማርቆስ የሌሎችን ትእዛዝ ተቀብሎ ለማገልገል ፈቃደኛ የሆነ አገልጋይ ነበር። ጳውሎስ ከመሞቱ ከጥቂት ጊዜ በፊት ማርቆስ ከእሱ ጋር የነበረ መሆኑ ይህን ሐዋርያ ጠቅሞት ሊሆን እንደሚችል ምንም ጥርጥር የለውም።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ