-
መጽሐፍ ቅዱስን መማርህን እንድትቀጥል ምን ሊረዳህ ይችላል?ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
-
-
5. የሚያጋጥምህን ተቃውሞ በጽናት ተቋቋም
አንዳንድ ጊዜ ሌሎች ሰዎች መጽሐፍ ቅዱስን መማርህን እንድታቆም ተጽዕኖ ሊያሳድሩብህ ይሞክራሉ። ፍራንሲስኮ የተባለ ሰው ያጋጠመውን ነገር ተመልከት። ቪዲዮውን ተመልከቱ፤ ከዚያም በሚከተሉት ጥያቄዎች ላይ ተወያዩ፦
በቪዲዮው ላይ የፍራንሲስኮ ጓደኞችና ቤተሰቦች ፍራንሲስኮ ስለሚማረው ነገር ሲነግራቸው ምን ተሰማቸው?
መጽናቱ ምን ጥቅም አስገኝቶለታል?
ሁለተኛ ጢሞቴዎስ 2:24, 25ን አንብቡ፤ ከዚያም በሚከተሉት ጥያቄዎች ላይ ተወያዩ፦
ቤተሰቦችህና ጓደኞችህ ስለምትማረው ነገር ምን ይሰማቸዋል?
በዚህ ጥቅስ መሠረት አንድ ሰው መጽሐፍ ቅዱስን በመማርህ ቢቃወምህ ምላሽ መስጠት ያለብህ እንዴት ነው? ለምን?
-
-
ምሥራቹን ለሌሎች መናገር የምትችለው እንዴት ነው?ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
-
-
ለሌሎች ምሥራቹን ስትናገር የምትናገረው ነገር ብቻ ሳይሆን የምትናገርበት መንገድም ሊያሳስብህ ይገባል። ሁለተኛ ጢሞቴዎስ 2:24ን እና 1 ጴጥሮስ 3:15ን አንብቡ፤ ከዚያም በሚከተሉት ጥያቄዎች ላይ ተወያዩ፦
ከሌሎች ጋር ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ስትነጋገር በእነዚህ ጥቅሶች ላይ ያለውን ምክር ተግባራዊ ማድረግ የምትችለው እንዴት ነው?
አንዳንድ የቤተሰብህ አባላት ወይም ጓደኞችህ በምትናገረው ነገር ላይስማሙ ይችላሉ። በዚህ ጊዜ ምን ልታደርግ ትችላለህ? ምን ልታደርግስ አይገባም?
ሰዎች የምትናገረውን ነገር እንዲቀበሉ ከመጫን ይልቅ በዘዴ አንዳንድ ጥያቄዎችን መጠየቅ የተሻለ የሚሆነው ለምንድን ነው?
-