የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • መጽሐፍ ቅዱስን መማርህን እንድትቀጥል ምን ሊረዳህ ይችላል?
    ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
    • 5. የሚያጋጥምህን ተቃውሞ በጽናት ተቋቋም

      አንዳንድ ጊዜ ሌሎች ሰዎች መጽሐፍ ቅዱስን መማርህን እንድታቆም ተጽዕኖ ሊያሳድሩብህ ይሞክራሉ። ፍራንሲስኮ የተባለ ሰው ያጋጠመውን ነገር ተመልከት። ቪዲዮውን ተመልከቱ፤ ከዚያም በሚከተሉት ጥያቄዎች ላይ ተወያዩ፦

      ቪዲዮ፦ ጽናት የሚያስገኘው ወሮታ (5:22)

      ‘ጽናት የሚያስገኘው ወሮታ’ ከተባለው ቪዲዮ ላይ የተወሰደ ትዕይንት። ፍራንሲስኮ ለቅርብ ጓደኞቹ ከእነሱ ጋር ያለውን ግንኙነት እንደሚያቆም ነግሯቸው ሲሄድ
      • በቪዲዮው ላይ የፍራንሲስኮ ጓደኞችና ቤተሰቦች ፍራንሲስኮ ስለሚማረው ነገር ሲነግራቸው ምን ተሰማቸው?

      • መጽናቱ ምን ጥቅም አስገኝቶለታል?

      ሁለተኛ ጢሞቴዎስ 2:24, 25⁠ን አንብቡ፤ ከዚያም በሚከተሉት ጥያቄዎች ላይ ተወያዩ፦

      • ቤተሰቦችህና ጓደኞችህ ስለምትማረው ነገር ምን ይሰማቸዋል?

      • በዚህ ጥቅስ መሠረት አንድ ሰው መጽሐፍ ቅዱስን በመማርህ ቢቃወምህ ምላሽ መስጠት ያለብህ እንዴት ነው? ለምን?

  • ምሥራቹን ለሌሎች መናገር የምትችለው እንዴት ነው?
    ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
    • ለሌሎች ምሥራቹን ስትናገር የምትናገረው ነገር ብቻ ሳይሆን የምትናገርበት መንገድም ሊያሳስብህ ይገባል። ሁለተኛ ጢሞቴዎስ 2:24⁠ን እና 1 ጴጥሮስ 3:15⁠ን አንብቡ፤ ከዚያም በሚከተሉት ጥያቄዎች ላይ ተወያዩ፦

      • ከሌሎች ጋር ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ስትነጋገር በእነዚህ ጥቅሶች ላይ ያለውን ምክር ተግባራዊ ማድረግ የምትችለው እንዴት ነው?

      • አንዳንድ የቤተሰብህ አባላት ወይም ጓደኞችህ በምትናገረው ነገር ላይስማሙ ይችላሉ። በዚህ ጊዜ ምን ልታደርግ ትችላለህ? ምን ልታደርግስ አይገባም?

      • ሰዎች የምትናገረውን ነገር እንዲቀበሉ ከመጫን ይልቅ በዘዴ አንዳንድ ጥያቄዎችን መጠየቅ የተሻለ የሚሆነው ለምንድን ነው?

      አንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ተማሪ ከመጽሐፍ ቅዱስ ላይ ያገኘውን ሐሳብ ለዘመዱ ሲናገር
አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ