-
ለክርስቲያኖች ተስፋ መልሕቅ፣ ፍቅር ደግሞ የሚገፋፋ ኃይል ሊሆንላቸው ይገባልመጠበቂያ ግንብ—1999 | ሐምሌ 15
-
-
ከመልሕቅ ጋር የተመሳሰለው ተስፋ
10, 11. ጳውሎስ ተስፋችንን ከምን ነገር ጋር አመሳስሎታል? ይህስ ንጽጽር ተገቢ የነበረው ለምንድን ነው?
10 ይሖዋ በአብርሃም በኩል ሰዎችን ለመባረክ ቃል መግባቱን ጳውሎስ አመልክቷል። ከዚያም ሐዋርያው እንዲህ አለ:- “እግዚአብሔር ሊዋሽ በማይቻል በሁለት በማይለወጥ ነገር [በቃሉና በመሐላው]፣ በፊታችን ያለውን ተስፋ ለመያዝ ለሸሸን ለእኛ ብርቱ መጽናናት ይሆንልን ዘንድ፣ በመሐላ በመካከል ገባ፤ ይህም ተስፋ እንደ ነፍስ መልሕቅ አለን እርሱም እርግጥና ጽኑ የሆነ . . . ነው።” (ዕብራውያን 6:17-19፤ ዘፍጥረት 22:16-18) ቅቡዓን ክርስቲያኖች የማይሞት ሰማያዊ ሕይወት የማግኘት ተስፋ አላቸው። በዛሬው ጊዜ የሚገኙ አብዛኞቹ የይሖዋ አገልጋዮች ገነት በሆነች ምድር ላይ የመኖር አስደናቂ ተስፋ አላቸው። (ሉቃስ 23:43) እንዲህ የመሰለው ተስፋ ባይኖር ኖሮ እምነት ያለው ሰው ባልተገኘ ነበር።
11 መልሕቅ መርከቡ በአንድ ቦታ ረግቶ እንዲቆይ ወይም እንዳይዋልል ለመከላከል የሚያገለግል በጣም አስፈላጊ የሆነ ጠንካራ የአደጋ መከላከያ ነው። ማንኛውም መርከበኛ መልሕቅ ሳይዝ ከወደብ አይንቀሳቀስም። ጳውሎስ በተደጋጋሚ ጊዜያት የመርከብ መሰበር አጋጥሞት ስለነበር የመርከበኞች ሕይወት በአብዛኛው የተመካው በመርከባቸው መልሕቅ ላይ መሆኑን ከተሞክሮ ያውቅ ነበር። (ሥራ 27:29, 39, 40፤ 2 ቆሮንቶስ 11:25) በመጀመሪያው መቶ ዘመን አንድ የመርከብ ካፕቴን መርከቡን እንደ ልቡ እንዲያሽከረክር የሚያስችለው ሞተር አልነበረውም። በመቅዘፊያ ይጠቀሙ ከነበሩ የጦር መርከቦች በስተቀር ሌሎች መርከቦች የሚንቀሳቀሱት በነፋስ ኃይል ነበር። አንድ መርከብ ከዓለት ጋር የመላተም አደጋ የሚያሰጋው ከሆነ የመርከቡ ካፕቴን ያለው ብቸኛ አማራጭ መልሕቁ ከባህሩ በታች ባለው መሬት ላይ ተቸክሎ እንደሚቆይ በመተማመን መልሕቁን ጥሎ ማዕበሉን ማሳለፍ ነው። ስለዚህ ጳውሎስ የአንድን ክርስቲያን ተስፋ ‘ከተረጋገጠና ጽኑ ከሆነ የነፍስ መልሕቅ’ ጋር አመሳስሎታል። (ዕብራውያን 6:19) የተቃውሞ ማዕበል ሲያናውጠን ወይም ሌሎች ፈተናዎች ሲያጋጥሙን የእምነት መርከባችን አደገኛ በሆኑት የጥርጣሬ ደለሎች ወይም አስከፊ መዘዝ ባላቸው የክህደት ዓለቶች እንዳይመታ በመከላከል ሕያው ነፍሳት ሆነን እንድንጸና የሚረዳን እንደ መልሕቅ የሆነው ነገር አስደናቂው ተስፋችን ነው።—ዕብራውያን 2:1፤ ይሁዳ 8-13
12. ይሖዋን ከመካድ ልንርቅ የምንችለው እንዴት ነው?
12 ጳውሎስ ዕብራውያን ክርስቲያኖችን “ወንድሞች ሆይ፣ ምናልባት ሕያው እግዚአብሔርን የሚያስክዳችሁ ክፉና የማያምን ልብ ከእናንተ በአንዳችሁ እንዳይኖር ተጠንቀቁ” ብሏቸዋል። (ዕብራውያን 3:12) በግሪክኛው ጥቅስ ላይ ‘መክዳት’ የሚለው ቃል በቀጥታ ሲተረጎም “መራቅ” ማለትም ከሃዲ መሆን ማለት ነው። ሆኖም እንዲህ ካለው የመርከብ መሠበር አደጋ ልንጠበቅ እንችላለን። እምነትና ተስፋ ሌላው ቀርቶ እጅግ አስከፊ የሆኑ የፈተና ማዕበሎች በሚያጋጥሙን ወቅት እንኳ ይሖዋን ሙጥኝ እንድንል ያስችሉናል። (ዘዳግም 4:4፤ 30:19, 20) እምነታችን በከሃዲዎች ትምህርት ነፋስ ወዲያና ወዲህ እንደሚገፋ መርከብ አይሆንም። (ኤፌሶን 4:13, 14) ተስፋችንን መልሕቅ በማድረግ ደግሞ የይሖዋ አገልጋዮች በመሆናችን የሚያጋጥሙንን የሕይወት ማዕበሎች ለመቋቋም እንችላለን።
-
-
ለክርስቲያኖች ተስፋ መልሕቅ፣ ፍቅር ደግሞ የሚገፋፋ ኃይል ሊሆንላቸው ይገባልመጠበቂያ ግንብ—1999 | ሐምሌ 15
-
-
ወደ መድረሻችን መገስገስ!
18. ወደፊት በእምነታችን ላይ የሚመጡትን ፈተናዎች በጽናት ለማሳለፍ የሚያስችለን ምንድን ነው?
18 ወደ አዲሱ የነገሮች ሥርዓት ከመግባታችን በፊት እምነታችንና ፍቅራችን ከባድ የሆነ ፈተና ሊያጋጥመው ይችላል። ሆኖም ይሖዋ “እርግጥና ጽኑ የሆነ” መልሕቅ ማለትም አስደናቂ ተስፋ ሰጥቶናል። (ዕብራውያን 6:19፤ ሮሜ 15:4, 13) ተቃውሞ ወይም ሌሎች ፈተናዎች በሚያጋጥሙን ጊዜ መልሕቅ የሆነውን ተስፋችን ቆንጥጠን ከያዝን መጽናት እንችላለን። አንደኛው ማዕበል አለፈ ብለን ሳንዘናጋ ተስፋችንን ለመገንባትና እምነታችንን ለማጠናከር ቁርጥ ውሳኔ እናድርግ።
-