-
እስከ መጨረሻው መጽናት ትችላላችሁመጠበቂያ ግንብ—1999 | ጥቅምት 1
-
-
10 ክርስቲያኖች ለሕይወት በሚያደርጉት ሩጫ ተመልካቾቹ እነማን ናቸው? ጳውሎስ በዕብራውያን ምዕራፍ 11 ላይ በቅድመ ክርስትና ዘመን ይኖሩ የነበሩ የታመኑ የይሖዋ ምሥክሮችን ከዘረዘረ በኋላ “እንግዲህ እነዚህን የሚያህሉ ምስክሮች እንደ ደመና በዙሪያችን ካሉልን፣ . . . በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት [“በጽናት፣” NW] እንሩጥ” ሲል ጽፏል። (ዕብራውያን 12:1) ጳውሎስ ደመናን ምሳሌ አድርጎ ሲጠቅስ የተጠቀመበት ግሪክኛ ቃል የተወሰነ መጠንና ቅርፅ ያለውን ደመና የሚያመለክተውን ቃል አይደለም። ከዚያ ይልቅ የመዝገበ ቃላት አዘጋጅ በሆኑት በደብልዩ ኢ ቫይን አባባል መሠረት “ሰማያትን የሸፈነውን ቅርጽ አልባ የደመናት ስብስብ የሚያመለክት” ቃል ተጠቅሟል። በግልጽ ለማየት እንደሚቻለው ጳውሎስ በአእምሮው የያዘው እንደ ትልቅ የደመና ክምችት ብዙ ቁጥር ያላቸውን ምሥክሮች ነበር።
11, 12. (ሀ) በቅድመ ክርስትና ዘመን ይኖሩ የነበሩ የታመኑ ምሥክሮች በጽናት እንድንሮጥ ድጋፍ ይሰጡናል የምንለው በምን መንገድ ነው? (ለ) ‘ከታላቁ የምሥክሮች ደመና’ ሙሉ በሙሉ ልንጠቀም የምንችለው እንዴት ነው?
11 በቅድመ ክርስትና ዘመን ይኖሩ የነበሩ የታመኑ ምሥክሮች ቃል በቃል ዘመናዊ ተመልካቾች መሆን ይችላሉ? አይችሉም። ሁሉም በሞት አንቀላፍተው ትንሣኤያቸውን በመጠባበቅ ላይ ናቸው። ይሁን እንጂ በሕይወት እያሉ የተሳካላቸው ሯጮች የነበሩ ሲሆን ሕያው ምሳሌነታቸውም በመጽሐፍ ቅዱስ ገጾች ላይ ሰፍሮ ይገኛል። ቅዱሳን ጽሑፎችን በምናጠናበት ጊዜ እነዚህ የታመኑ ሰዎች በአእምሯችን ውስጥ ሕይወት ሊዘሩና በሩጫው እስከ ፍጻሜው እንድንገፋ ሊያበረታቱን ይችላሉ ብሎ ለመናገር ይቻላል።—ሮሜ 15:4a
12 ለምሳሌ ያህል በዓለም ያሉ ነገሮች በሚያጓጉን ጊዜ ሙሴ የግብጽን ክብር ስለ መተዉ የሚናገረውን ታሪክ መመርመራችን በሩጫው እንድንቀጥል አይገፋፋንምን? በጣም ከባድ መከራ የደረሰብን ሲመስለን አብርሃም ልጁን ይስሐቅን መሥዋዕት አድርጎ እንዲያቀርብ በተጠየቀ ጊዜ ያጋጠመውን ከባድ ፈተና ማስታወሳችን ለእምነት በምናደርገው ትግል እጃችንን እንዳንሰጥ እንደሚያበረታን የተረጋገጠ ነው። የእነዚህ ምሥክሮች ‘ታላቅ ደመና’ በዚህ መንገድ የሚሰጠን ማበረታቻና ድጋፍ የተመካው በማስተዋል ዓይናችን እነሱን በግልጽ በመመልከታችን ላይ ነው።
13. ለሕይወት በሚደረገው ሩጫ በጊዜያችን የሚገኙ የይሖዋ ምሥክሮች ማነቃቂያና ድጋፍ የሚሆኑን በምን መንገድ ነው?
13 በተጨማሪም በዛሬው ጊዜ ብዙ ቁጥር ባላቸው የይሖዋ ምሥክሮች መካከል እንገኛለን። ቅቡዓን ክርስቲያኖችና የ“እጅግ ብዙ ሰዎች” ክፍል አባላት የሆኑ ወንዶችና ሴቶች ግሩም የእምነት ምሳሌዎችን ትተው አልፈዋል! (ራእይ 7:9) በዚህ መጽሔትና በሌሎች የመጠበቂያ ግንብ ማኅበር ጽሑፎች ላይ በየጊዜው የሚወጣውን የሕይወት ታሪካቸውን ማንበብ እንችላለን።b በእምነታቸው ላይ ስናሰላስል እስከ መጨረሻው ለመጽናት የሚያስችል ማበረታቻ እናገኛለን። እንዲሁም ይሖዋን በታማኝነት በማገልገል ላይ ካሉ የቅርብ ወዳጆቻችንና ዘመዶቻችን የምናገኘው ድጋፍ እንዴት አስደናቂ ነው! አዎን፣ ለሕይወት በሚደረገው ሩጫ ማበረታቻና ድጋፍ የሚሰጡን ብዙ ናቸው።
ፍጥነትህን በጥበብ መጥን
14, 15. (ሀ) ፍጥነታችንን በጥበብ መመጠን ያለብን ለምንድን ነው? (ለ) ግብ ስናወጣ ምክንያታዊ መሆን ያለብን ለምንድን ነው?
14 እንደ ማራቶን ባለው የረዥም ርቀት ሩጫ ላይ አንድ ሯጭ ፍጥነቱን በጥበብ መመጠን አለበት። ኒው ዮርክ ራነር የተባለው መጽሔት “ከመነሻው ጀምሮ በከፍተኛ ፍጥነት መሮጥ ጥረትህን መና ሊያስቀረው ይችላል” ብሏል። “በመጨረሻዎቹ ርቀቶች ላይ ከፍተኛ ትግል ለማድረግ አሊያም አቋርጦ ለመውጣት ትገደድ ይሆናል።” አንድ የማራቶን ሯጭ የሚከተለውን ያስታውሳል:- “ለውድድሩ በምንዘጋጅበት ወቅት ትምህርት ይሰጡን ከነበሩት መካከል አንደኛው እንዲህ ሲል በግልጽ አስጠነቀቀን:- ‘ፈጣን ሯጮችን አትከተሉ። የራሳችሁን ፍጥነት ጠብቃችሁ ሩጡ። ካለበለዚያ ትዝሉና አቋርጣችሁ ለመውጣት ትገደዱ ይሆናል።’ ይህን ምክር መከተሌ ሩጫውን ለመጨረስ ረድቶኛል።”
15 ለሕይወት በሚደረገው ሩጫ የአምላክ አገልጋዮች ከፍተኛ ተጋድሎ ማድረግ አለባቸው። (ሉቃስ 13:24) ይሁን እንጂ ደቀ መዝሙሩ ያዕቆብ “ላይኛይቱ ጥበብ . . . ምክንያታዊ . . . ናት” ሲል ጽፏል። (ያዕቆብ 3:17NW) የሌሎች መልካም ምሳሌነት የበለጠ እንድናደርግ ሊያበረታታን ቢችልም ምክንያታዊነት ከችሎታችንና ከሁኔታችን ጋር የሚጣጣሙ ተጨባጭ ግቦችን ለማውጣት ሊረዳን ይችላል። ቅዱሳን ጽሑፎች እንደሚከተለው በማለት ያሳስቡናል:- “ነገር ግን እያንዳንዱ የገዛ ራሱን ሥራ ይፈትን፣ ከዚያም በኋላ ስለ ሌላው ሰው ያልሆነ ስለ ራሱ ብቻ የሚመካበትን ያገኛል፤ እያንዳንዱ የገዛ ራሱን ሸክም ሊሸከም ነውና።”—ገላትያ 6:4, 5
16. ቦታን መጠበቅ ፍጥነታችንን ለመመጠን የሚረዳን እንዴት ነው?
16 በሚክያስ 6:8 ላይ የሚከተለውን በጥልቀት እንድናስብ የሚያደርግ ጥያቄ ተጠይቀናል:- “እግዚአብሔርም ከአንተ የሚሻው ምንድር ነው? . . . ከአምላክህም ጋር በትሕትና [“ቦታህን ጠብቀህ፣” NW] ትሄድ ዘንድ አይደለምን?” ቦታን መጠበቅ ያለብንን የአቅም ገደብ መገንዘብን ይጨምራል። የጤና መታወክ ወይም የእድሜ መግፋት ለአምላክ የምናቀርበውን አገልግሎት በተወሰነ ደረጃ ገድበውት ይሆን? ተስፋ አንቁረጥ። ይሖዋ ‘በሌለን መጠን ሳይሆን ባለን መጠን’ የምናደርገውን ጥረትና የምናቀርበውን መሥዋዕት ይቀበላል።—2 ቆሮንቶስ 8:12፤ ከሉቃስ 21:1-4 ጋር አወዳድር።
-
-
እስከ መጨረሻው መጽናት ትችላላችሁመጠበቂያ ግንብ—1999 | ጥቅምት 1
-
-
መጨረሻው እየቀረበ ሲመጣ
20. ለሕይወት የሚደረገው ሩጫ ወደ መጨረሻው እየቀረበ ሲመጣ ይበልጥ አስቸጋሪ የሚሆነው እንዴት ሊሆን ይችላል?
20 ለሕይወት በሚደረገው ሩጫ ከቀንደኛው ጠላታችን ከሰይጣን ዲያብሎስ ጋር መታገል አለብን። ወደ መጨረሻው እየተቃረብን ስንመጣ ከሩጫው ተደናቅፈን እንድንወጣ ወይም ፍጥነታችንን እንድንቀንስ ለማድረግ የማይፈነቅለው ድንጋይ የለም። (ራእይ 12:12, 17) ጦርነት፣ ረሃብ፣ ወረርሽኝና ይህን ‘የፍጻሜ ዘመን’ ለይተው የሚያሳውቁ ሌሎች ችግሮች እያሉ ራስን የወሰኑ የመንግሥቱ አዋጅ ነጋሪ ሆኖ በታማኝነት መቀጠል ቀላል አይደለም። (ዳንኤል 12:4፤ ማቴዎስ 24:3-14፤ ሉቃስ 21:11፤ 2 ጢሞቴዎስ 3:1-5) ከዚህም በላይ ሩጫውን የጀመርነው ከአሥርተ ዓመታት በፊት ከሆነ አንዳንድ ጊዜ መጨረሻው እኛ ከምናስበው ይበልጥ የራቀ ሊመስለን ይችላል። ይሁንና መጨረሻው እንደሚመጣ የአምላክ ቃል ማረጋገጫ ይሰጠናል። ይሖዋ ቀኑ አይዘገይም ብሏል። መጨረሻው እጅግ ቀርቧል።—ዕንባቆም 2:3፤ 2 ጴጥሮስ 3:9, 10
21. (ሀ) ለሕይወት በምናደርገው ሩጫ ለመቀጠል ምን ሊያጠነክረን ይችላል? (ለ) መጨረሻው እየቀረበ ሲመጣ ቁርጥ ውሳኔያችን ምን ማድረግ መሆን አለበት?
21 እንግዲያው ለሕይወት በሚደረገው ሩጫ ስኬታማ እንድንሆን ከፈለግን ይሖዋ እኛን በመንፈሳዊ ነገሮች ለመመገብ ባደረገው ፍቅራዊ ዝግጅት በመጠቀም ጥንካሬ ለማግኘት መጣር አለብን። በተጨማሪም በዚህ ሩጫ ተካፋዮች ከሆኑት የእምነት አጋሮቻችን ጋር አዘውትረን ከመሰብሰብ የምናገኘው ማበረታቻም በእጅጉ ያስፈልገናል። በመንገዳችን ላይ የሚገጥሙን ከባድ መከራዎችና ያልተጠበቁ አጋጣሚዎች ሩጫችንን ይበልጥ አስቸጋሪ ቢያደርጉብን እንኳ ይሖዋ “ከወትሮው የበለጠ ኃይል” ስለሚሰጠን እስከ ፍጻሜው ልንጸና እንችላለን። (2 ቆሮንቶስ 4:7 NW) ይሖዋ ሩጫችንን በአሸናፊነት እንድንደመድም የሚፈልግ መሆኑን ማወቃችን ምንኛ የሚያጽናና ነው! ‘ባንዝል በጊዜው እንደምናጭድ’ ሙሉ በሙሉ በመተማመን ‘በፊታችን ያለውን ሩጫ በጽናት ለመሮጥ’ ቁርጥ ውሳኔያችን ይሁን።—ዕብራውያን 12:1፤ ገላትያ 6:9
-