የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ሥራና ስለ ገንዘብ ምን ይላል?
    ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
    • 2. ለገንዘብ ሊኖረን የሚገባው ሚዛናዊ አመለካከት ምንድን ነው?

      መጽሐፍ ቅዱስ “ገንዘብ ጥበቃ እንደሚያስገኝ” ይናገራል፤ በሌላ በኩል ግን ገንዘብ ብቻውን ደስተኛ ሊያደርገን እንደማይችል ያስጠነቅቃል። (መክብብ 7:12) የአምላክ ቃል ገንዘብ እንዳንወድ፣ ከዚህ ይልቅ ‘ባሉን ነገሮች ረክተን እንድንኖር’ የሚያበረታታን ለዚህ ነው። (ዕብራውያን 13:5⁠ን አንብብ።) ባሉን ነገሮች ረክተን የምንኖር ከሆነ ‘ተጨማሪ ነገር ማግኘት አለብኝ’ የሚለው ስሜት ከሚያስከትለው ብስጭት ነፃ እንሆናለን። አላስፈላጊ ዕዳ ውስጥ ከመግባት እንድናለን። (ምሳሌ 22:7) በተጨማሪም ቁማር ከመጫወትና በአጭር ጊዜ ለመክበር ያስችላሉ የሚባሉ የንግድ አማራጮችን ከማሳደድ እንቆጠባለን።

  • መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ሥራና ስለ ገንዘብ ምን ይላል?
    ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
    • 5. ባሉን ነገሮች ረክተን መኖራችን ይጠቅመናል

      በርካታ ሰዎች የቻሉትን ያህል ብዙ ገንዘብ ለማጠራቀም ይሞክራሉ። መጽሐፍ ቅዱስ ግን ከዚህ የተለየ ነገር እንድናደርግ ይመክረናል። አንደኛ ጢሞቴዎስ 6:6-8⁠ን አንብቡ፤ ከዚያም በሚከተለው ጥያቄ ላይ ተወያዩ፦

      • መጽሐፍ ቅዱስ ምን እንድናደርግ ይመክረናል?

      ያለን ገንዘብ በጣም አነስተኛ ቢሆንም እንኳ ደስተኛ መሆን እንችላለን። ቪዲዮውን ተመልከቱ፤ ከዚያም በሚከተለው ጥያቄ ላይ ተወያዩ፦

      ቪዲዮ፦ “ባሏችሁ ነገሮች ረክታችሁ ኑሩ” (3:20)

      • በቪዲዮው ላይ የታዩት ቤተሰቦች ያላቸው ገንዘብ ጥቂት ቢሆንም ደስተኛ እንዲሆኑ የረዳቸው ምንድን ነው?

      ብዙ ገንዘብ እያለንም ተጨማሪ ገንዘብ ለማግኘት የምንፈልግ ቢሆንስ? ኢየሱስ ይህ ያለውን አደጋ የሚያሳይ ምሳሌ ተናግሯል። ሉቃስ 12:15-21⁠ን አንብቡ፤ ከዚያም በሚከተለው ጥያቄ ላይ ተወያዩ፦

      • ኢየሱስ ከሰጠው ምሳሌ ምን ትምህርት አግኝተሃል?—ቁጥር 15⁠ን ተመልከት።

      ምሳሌ 10:22⁠ን እና 1 ጢሞቴዎስ 6:10⁠ን አንብቡና አወዳድሩ። ከዚያም በሚከተሉት ጥያቄዎች ላይ ተወያዩ፦

      • ይበልጥ አስፈላጊ የሆነው ምን ይመስልሃል? የይሖዋ ወዳጅ መሆን ወይስ ብዙ ገንዘብ ማግኘት? እንዲህ ብለህ የመለስከው ለምንድን ነው?

      • ገንዘብ ማሳደድ ምን ችግሮች ሊያስከትል ይችላል?

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ