-
ወደ አምላክ እረፍት ገብተሃል?መጠበቂያ ግንብ—2011 | ሐምሌ 15
-
-
“የአምላክ ቃል ሕያው” ነው
20. በዕብራውያን 4:12 ላይ የሚገኘውን ሐሳብ በየትኞቹ ሁለት መንገዶች ልንረዳው እንችላለን? (የግርጌ ማስታወሻውን ተመልከት።)
20 ጳውሎስ “የአምላክ ቃል ሕያው” እንደሆነ ሲጽፍ በዋነኝነት በጽሑፍ ስለሰፈረው የአምላክ ቃል ይኸውም ስለ መጽሐፍ ቅዱስ መናገሩ አልነበረም።c በጥቅሱ ዙሪያ ያለው ሐሳብ ጳውሎስ፣ አምላክ ስለሰጣቸው ተስፋዎች እየተናገረ እንደነበር ይጠቁማል። ጳውሎስ ሊናገረው የፈለገው ነጥብ፣ አምላክ ቃል የገባውን ነገር ሳይፈጽም የማይቀር መሆኑን ነው። ይሖዋ በነቢዩ ኢሳይያስ አማካኝነት እንደሚከተለው በማለት ይህን ገልጿል፦ “ቃሌ፣ በከንቱ ወደ እኔ አይመለስም፤ . . . የተላከበትንም ዐላማ ይፈጽማል።” (ኢሳ. 55:11) እንግዲያው ነገሮች እኛ እንደምንፈልገው ቶሎ ሳይፈጸሙ ሲቀሩ ትዕግሥት ማጣት አይኖርብንም። ይሖዋ ዓላማውን በተሳካ መንገድ ከዳር ለማድረስ ‘መሥራቱን’ ይቀጥላል።—ዮሐ. 5:17
21. በዕብራውያን 4:12 ላይ የሚገኘው ሐሳብ ‘የእጅግ ብዙ ሕዝብ’ አባል የሆኑ ታማኝ አረጋውያንን የሚያጽናናቸው እንዴት ነው?
21 ‘የእጅግ ብዙ ሕዝብ’ አባል የሆኑ ታማኝ አረጋውያን ለበርካታ ዓመታት ይሖዋን ሲያገለግሉት ቆይተዋል። (ራእይ 7:9) ከእነዚህ መካከል ብዙዎቹ በዚህ ሥርዓት ውስጥ እንደሚያረጁ ፈጽሞ አላሰቡም ነበር። ይሁንና ይህ መሆኑ ተስፋ አላስቆረጣቸውም። (መዝ. 92:14) አምላክ የገባው ቃል የሞተ ወይም ያበቃለት ነገር እንዳልሆነ ከዚህ ይልቅ ሕያው እንደሆነና ይሖዋም ቃሉን ለመፈጸም እየሠራ መሆኑን ይገነዘባሉ። አምላክ፣ ለዓላማው ትልቅ ቦታ ስለሚሰጠው እኛም ዓላማውን ከፍ አድርገን ስንመለከተው ደስ ይለዋል። ይሖዋ፣ ዓላማው እንደሚፈጸምና ሕዝቦቹም በቡድን ደረጃ ዓላማውን እንደሚደግፉ በእርግጠኝነት ስለሚያውቅ አሁን ባለንበት በዚህ በሰባተኛው ቀን እረፍት ላይ ነው ሊባል ይችላል። አንተስ ወደ አምላክ እረፍት ገብተሃል?
-
-
ወደ አምላክ እረፍት ገብተሃል?መጠበቂያ ግንብ—2011 | ሐምሌ 15
-
-
c በዛሬው ጊዜ አምላክ የሚያነጋግረን በጽሑፍ በሰፈረው ቃሉ ማለትም በመጽሐፍ ቅዱስ አማካኝነት ሲሆን መጽሐፍ ቅዱስ በሕይወታችን ላይ ተጽዕኖ ማሳደር ይችላል። በመሆኑም በዕብራውያን 4:12 ላይ የሚገኘው ጳውሎስ የተናገረው ሐሳብ መጽሐፍ ቅዱስን ለማመልከትም ሊሠራበት ይችላል።
-