-
እረኞች፣ ከሁሉ የላቁትን እረኞች አርዓያ ተከተሉመጠበቂያ ግንብ—2013 | ኅዳር 15
-
-
4. በዚህ የጥናት ርዕስ ላይ የሚብራራው ምንድን ነው?
4 ታዲያ ክርስቲያን እረኞች በጎቹን ሊይዟቸው የሚገባው እንዴት ነው? የጉባኤው አባላት “በመካከላችሁ ግንባር ቀደም ሆነው አመራር ለሚሰጧችሁ ታዘዙ” የሚል ማበረታቻ ተሰጥቷቸዋል። በሌላ በኩል ደግሞ ክርስቲያን ሽማግሌዎች “የአምላክ ንብረት በሆኑት ላይ [ሥልጣናቸውን]” ከማሳየት እንዲቆጠቡ ማሳሰቢያ ተሰጥቷቸዋል። (ዕብ. 13:17፤ 1 ጴጥሮስ 5:2, 3ን አንብብ።) ታዲያ የተሾሙ ሽማግሌዎች በመንጋው ላይ ሥልጣናቸውን ከማሳየት በመቆጠብ አመራር መስጠት የሚችሉት እንዴት ነው? በሌላ አባባል፣ ሽማግሌዎች አምላክ ለበላይ ተመልካቾች ከሰጠው ሥልጣን ሳያልፉ በጎቹ የሚያስፈልጓቸውን ነገሮች ማሟላት የሚችሉት እንዴት ነው?
-
-
እረኞች፣ ከሁሉ የላቁትን እረኞች አርዓያ ተከተሉመጠበቂያ ግንብ—2013 | ኅዳር 15
-
-
9. ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱ ምን ዓይነት አመለካከት እንዲኖራቸው አበረታቷል?
9 ኢየሱስ መንፈሳዊ እረኞች ያላቸውን ሚና በተመለከተ ያለው አመለካከት፣ በአንድ ወቅት ያዕቆብና ዮሐንስ ካሳዩት አመለካከት የተለየ ነበር። እነዚህ ሁለት ሐዋርያት በመንግሥቱ ውስጥ ላቅ ያለ ቦታ ለማግኘት ፈልገው ነበር። ኢየሱስ ግን እንዲህ በማለት አመለካከታቸውን እንዲያስተካክሉ ረድቷቸዋል፦ “የባዕድ አገር ገዢዎች በዙሪያቸው ያሉ ሰዎችን ማዘዝ እንደሚወዱ ታውቃላችሁ። ታላላቅ መሪዎቻቸውም በሚገዟቸው ሰዎች ሁሉ ላይ ሙሉ ሥልጣን አላቸው። እናንተ ግን እንደ እነሱ አትሁኑ። ታላቅ መሆን የምትፈልጉ ከሆነ የሌሎቹ ሁሉ አገልጋይ መሆን አለባችሁ።” (ማቴ. 20:25, 26 ኮንቴምፖራሪ ኢንግሊሽ ቨርዥን) ሐዋርያቱ በባልንጀሮቻቸው ላይ ‘ሥልጣናቸውን ለማሳየት’ ወይም ‘በዙሪያቸው ያሉ ሰዎችን ለማዘዝ’ ያላቸውን ፍላጎት ማስወገድ አስፈልጓቸው ነበር።
10. ኢየሱስ ሽማግሌዎች መንጋውን በምን መንገድ እንዲይዙ ይፈልጋል? በዚህ ረገድ ጳውሎስ ምን ምሳሌ ትቷል?
10 ኢየሱስ ክርስቲያን ሽማግሌዎች መንጋውን እሱ በያዘበት መንገድ እንዲይዙ ይፈልጋል። በባልንጀሮቻቸው ላይ እንደ ጌታ ከመሠልጠን ይልቅ የእነሱ አገልጋይ ለመሆን ፈቃደኛ መሆን አለባቸው። ሐዋርያው ጳውሎስ እንዲህ ዓይነት የትሕትና ባሕርይ አንጸባርቋል፤ በኤፌሶን ጉባኤ ለነበሩ ሽማግሌዎች የተናገረው የሚከተለው ሐሳብ ይህን ያሳያል፦ “በእስያ አውራጃ እግሬ ከረገጠበት ከመጀመሪያው ቀን አንስቶ በዚያ በቆየሁበት ጊዜ ሁሉ ከእናንተ እንዳልተለየሁ ታውቃላችሁ፤ . . . በታላቅ ትሕትናና በእንባ ጌታን አገለግል ነበር።” ሐዋርያው እነዚህ ሽማግሌዎች ሌሎችን ከልብ በመነጨ ስሜትና በትሕትና እንዲያገለግሉ ይፈልግ ነበር። “እናንተም እንዲሁ እየሠራችሁ ደካማ የሆኑትን መርዳት እንዳለባችሁ በሁሉም ነገር አሳይቻችኋለሁ” ብሏል። (ሥራ 20:18, 19, 35) ጳውሎስ የቆሮንቶስ ክርስቲያኖችን “በእምነታችሁ ላይ የምናዝ አይደለንም” ሲል ገልጾላቸዋል። ከዚህ ይልቅ ለደስታቸው ከእነሱ ጋር አብሮ እንደሚሠራ ተናግሯል። (2 ቆሮ. 1:24) ጳውሎስ ትሕትና በማሳየትና ተግቶ በመሥራት ረገድ በዛሬው ጊዜ ላሉ ሽማግሌዎች ግሩም ምሳሌ ትቷል።
-
-
እረኞች፣ ከሁሉ የላቁትን እረኞች አርዓያ ተከተሉመጠበቂያ ግንብ—2013 | ኅዳር 15
-
-
“ለመንጋው ምሳሌ” ሁኑ
ሽማግሌዎች የቤተሰባቸውን አባላት ለአገልግሎት እንዲዘጋጁ ይረዷቸዋል (አንቀጽ 13ን ተመልከት)
13, 14. አንድ ሽማግሌ ለመንጋው ምሳሌ መሆን የሚገባው በየትኞቹ መስኮች ነው?
13 ሐዋርያው ጴጥሮስ የጉባኤ ሽማግሌዎች በተሰጣቸው ‘መንጋ ላይ መሠልጠን’ እንደሌለባቸው ምክር ከሰጠ በኋላ “ለመንጋው ምሳሌ” እንዲሆኑ አበረታቷቸዋል። (1 ጴጥ. 5:3) አንድ ሽማግሌ ለመንጋው ምሳሌ መሆን የሚችለው እንዴት ነው? “የበላይ ተመልካች ለመሆን የሚጣጣር ማንኛውም ሰው” ሊያሟላቸው ከሚገቡ ብቃቶች መካከል ሁለቱን እንመልከት። በመጀመሪያ ደረጃ “ጤናማ አስተሳሰብ ያለው” መሆን አለበት፤ በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ “የራሱን ቤተሰብ በተገቢው ሁኔታ የሚያስተዳድር ሊሆን ይገባዋል።” አንድ ሽማግሌ ቤተሰብ ያለው ከሆነ ቤተሰቡን የሚያስተዳድርበት መንገድ ለሌሎች ምሳሌ ሊሆን ይገባል፤ “ደግሞስ አንድ ሰው የራሱን ቤተሰብ እንዴት እንደሚያስተዳድር ካላወቀ የአምላክን ጉባኤ እንዴት ሊንከባከብ ይችላል?” (1 ጢሞ. 3:1, 2, 4, 5) አንድ ወንድም ለበላይ ተመልካችነት ኃላፊነት ብቁ ለመሆን ጤናማ አስተሳሰብ ሊኖረው ይገባል ሲባል የመጽሐፍ ቅዱስን መሠረታዊ ሥርዓቶች በሚገባ ይረዳል እንዲሁም በሕይወቱ ውስጥ እንዴት ተግባራዊ እንደሚያደርጋቸው ያውቃል ማለት ነው። አስቸጋሪ ሁኔታዎች ሲያጋጥሙት በረጋ መንፈስ ያስባል እንጂ ለውሳኔ አይቸኩልም። የጉባኤው አባላት እነዚህን ባሕርያት በሽማግሌዎች ላይ ማየታቸው በእነሱ እንዲተማመኑ ያደርጋቸዋል።
14 በተጨማሪም የበላይ ተመልካቾች በመስክ አገልግሎት ግንባር ቀደም በመሆን ለእምነት ባልንጀሮቻቸው ጥሩ ምሳሌ ይሆናሉ። በዚህ ረገድ ኢየሱስ ለበላይ ተመልካቾች ግሩም ምሳሌ ትቷል። ኢየሱስ ምድር ላይ በነበረበት ወቅት የመንግሥቱን ምሥራች ለመስበኩ ሥራ ትልቅ ቦታ ሰጥቷል። ከዚህም ሌላ ሥራው እንዴት መከናወን እንዳለበት ለደቀ መዛሙርቱ አሳይቷቸዋል። (ማር. 1:38፤ ሉቃስ 8:1) በዛሬው ጊዜ አስፋፊዎች ከሽማግሌዎች ጋር አብረው ሲያገለግሉ፣ ሽማግሌዎች ለዚህ ሕይወት አድን ሥራ ያላቸውን ቅንዓት ሲመለከቱና የሚያስተምሩበትን መንገድ በትኩረት በመከታተል ትምህርት ሲቀስሙ በጣም ይበረታታሉ! የበላይ ተመልካቾች የተጣበበ ፕሮግራም ቢኖራቸውም ምሥራቹን ለመስበክ ጊዜያቸውንና ጉልበታቸውን መሥዋዕት ለማድረግ የሚያሳዩት ቁርጠኝነት ጉባኤው በአጠቃላይ ተመሳሳይ ቅንዓት ለማሳየት እንዲነሳሳ ያደርጋል። በተጨማሪም ሽማግሌዎች ለጉባኤ ስብሰባዎች በመዘጋጀትና ተሳትፎ በማድረግ እንዲሁም የመንግሥት አዳራሹን እንደ ማጽዳትና መጠገን በመሳሰሉ ሌሎች እንቅስቃሴዎች በመካፈል ለወንድሞቻቸው ጥሩ ምሳሌ መሆን ይችላሉ።—ኤፌ. 5:15, 16፤ ዕብራውያን 13:7ን አንብብ።
የበላይ ተመልካቾች በመስክ አገልግሎት በሚያደርጉት ተሳትፎ ለሌሎች ግሩም ምሳሌ ይሆናሉ (አንቀጽ 14ን ተመልከት)
-