-
እንዴት ዓይነት ሰዎች ልትሆኑ ይገባችኋል?የመንግሥት አገልግሎት—1995 | ነሐሴ
-
-
1 የሰው ልጆች በጠቅላላ ላደረጉት ነገር መልስ የሚሰጡበት ጊዜ ቀርቧል። መጽሐፍ ቅዱስ ይህንን ጊዜ ‘የእግዚአብሔር ቀን’ በማለት ይጠራዋል። ይህ ቀን በክፉዎች ላይ መለኮታዊ ፍርድ የሚሰጥበትና ጻድቃን ነፃ የሚወጡበት ጊዜ ነው። በዚያን ጊዜ በሕይወት የሚኖሩ ሰዎች ሁሉ ይከተሉት ስለነበረው የሕይወት ጎዳና መልስ ይሰጣሉ። ጴጥሮስ ይህንን በአእምሮው በመያዝ “እንዴት ዓይነት ሰዎች ልትሆኑ ይገባችኋል?” በማለት ራሳችንን እንድንመረምር የሚያደርግ አንድ ጥያቄ አቅርቧል። ‘ቅዱስ የሆነ አኗኗርን፣ ለአምላክ ማደርን የሚያሳዩ ተግባራትንና የይሖዋን ቀን አቅርቦ የመመልከትን’ ጠቀሜታም ሆነ ‘ነውርና ነቀፋ የሌለብን የመሆንንና በሰላም የመገኘትን’ አስፈላጊነት ጠበቅ አድርጎ ገልጿል።— 2 ጴጥ. 3:11–14
-
-
እንዴት ዓይነት ሰዎች ልትሆኑ ይገባችኋል?የመንግሥት አገልግሎት—1995 | ነሐሴ
-
-
5 ያለ ነውር፣ ያለ ነቀፋ መሆንና በሰላም መገኘት፦ ከእጅግ ብዙ ሰዎች መካከል እንደመሆናችን መጠን ‘ልብሳችንን አጥበን በበጉ ደም አንጽተናል።’ (ራእይ 7:14) ስለዚህ “ያለ ነውር” መሆን ማለት ለአምላክ በወሰንነው ንጹሕ ሕይወት ላይ የዓለም ቆሻሻዎች እንዳይፈናጠቁበት አጥብቀን መከላከል አለብን ማለት ነው። አምላካዊ ያልሆኑ ቁሳዊ ነገሮችን ማሳደድ ክርስቲያናዊ ጠባያችንን እንዳያጎድፈው በመከላከል “ያለ ነቀፋ” ሆነን መገኘት አንችላለን። (ያዕ. 1:27፤ 1 ዮሐ. 2:15–17) ከሌሎች ጋር ባለን ግንኙነት ሁሉ ‘የአምላክን ሰላም’ በማንፀባረቅ “በሰላም” እንደምንኖር እናሳያለን።— ፊልጵ. 4:7፤ ሮሜ 12:18፤ 14:19
-