የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • መጽሐፍ ቅዱስ የአምላክ ቃል ነው
    ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
    • 1. መጽሐፍ ቅዱስን የጻፉት ሰዎች ከሆኑ የአምላክ ቃል ነው ሊባል የሚችለው እንዴት ነው?

      መጽሐፍ ቅዱስን የጻፉት 40 የሚሆኑ ሰዎች ናቸው፤ የተጻፈውም ከ1513 ዓ.ዓ. እስከ 98 ዓ.ም. ድረስ ባሉት 1,600 ዓመታት ገደማ ውስጥ ነው። ጸሐፊዎቹ የተለያየ አስተዳደግና የኑሮ ደረጃ ያላቸው ናቸው። ያም ቢሆን ሁሉም የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች እርስ በርስ ይስማማሉ። ይህ ሊሆን የቻለው እንዴት ነው? መጽሐፍ ቅዱስ የአምላክ ቃል ስለሆነ ነው። (1 ተሰሎንቄ 2:13⁠ን አንብብ።) ጸሐፊዎቹ የመዘገቡት የራሳቸውን ሐሳብ አይደለም። ከዚህ ይልቅ ‘ከአምላክ የተቀበሉትን በመንፈስ ቅዱስ ተገፋፍተው ተናግረዋል።’a (2 ጴጥሮስ 1:21) አምላክ ሰዎች የእሱን ሐሳብ እንዲጽፉ ለመምራት ወይም ለማነሳሳት መንፈስ ቅዱስን ተጠቅሟል።—2 ጢሞቴዎስ 3:16

  • ይሖዋ ምን ዓይነት አምላክ ነው?
    ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
    • 4. መንፈስ ቅዱስ—አምላክ የተለያዩ ሥራዎችን ለማከናወን የሚጠቀምበት ኃይል

      በአምላክ መንፈስ ቅዱስ አማካኝነት የተከናወኑትን ነገሮች የሚያሳዩ ሥዕሎች፦ 1. ፕላኔቶችና ጽንፈ ዓለም 2. አንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ጸሐፊ በአምላክ መንፈስ እየተመራ ጥቅልል ላይ ሲጽፍ

      የተለያዩ ሥራዎችን ለማከናወን እጃችንን እንደምንጠቀም ሁሉ ይሖዋም ቅዱስ መንፈሱን ይጠቀማል። መንፈስ ቅዱስ ራሱን የቻለ አካል ሳይሆን አምላክ የተለያዩ ነገሮችን ለማከናወን የሚጠቀምበት ኃይል እንደሆነ መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል። ሉቃስ 11:13⁠ን እና የሐዋርያት ሥራ 2:17⁠ን አንብቡ፤ ከዚያም በሚከተሉት ጥያቄዎች ላይ ተወያዩ፦

      • አምላክ፣ ቅዱስ መንፈሱን ለማግኘት በሚጠይቁት ሰዎች ላይ ይህን መንፈስ ‘ያፈስሳል።’ ታዲያ መንፈስ ቅዱስ ራሱን የቻለ አካል ነው ወይስ አምላክ የተለያዩ ነገሮችን ለማከናወን የሚጠቀምበት ኃይል? እንዲህ ብለህ የመለስከው ለምንድን ነው?

      ይሖዋ አስደናቂ ነገሮችን ለማከናወን ቅዱስ መንፈሱን ይጠቀማል። መዝሙር 104:30⁠ን እና 2 ጴጥሮስ 1:20, 21⁠ን አንብቡ፤ ከዚያም በሚከተለው ጥያቄ ላይ ተወያዩ፦

      • ይሖዋ መንፈስ ቅዱስን የተጠቀመባቸው አንዳንድ መንገዶች የትኞቹ ናቸው?

      በአምላክ መንፈስ ቅዱስ አማካኝነት የተከናወኑትን ነገሮች የሚያሳዩ ሥዕሎች፦ 1. ፕላኔቶችና ጽንፈ ዓለም 2. አንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ጸሐፊ በአምላክ መንፈስ እየተመራ ጥቅልል ላይ ሲጽፍ
አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ