-
ከሐሰተኛ አስተማሪዎች ተጠንቀቁ!መጠበቂያ ግንብ—1997 | መስከረም 1
-
-
3. ጴጥሮስ እንደገና እንደሚፈጸም የተናገረለት ጥንት የተፈጸመ ምን ነገር አለ?
3 ጴጥሮስ ወንድሞቹ ትንቢታዊውን ቃል በትኩረት እንዲከታተሉ ካሳሰበ በኋላ እንዲህ ብሏል:- “ነገር ግን ሐሰተኞች ነቢያት ደግሞ በሕዝቡ መካከል [በጥንቱ እስራኤል መካከል] ነበሩ እንዲሁም በመካከላችሁ ደግሞ ሐሰተኞች አስተማሪዎች ይሆናሉ።” (2 ጴጥሮስ 1:14–2:1) ጥንት የነበሩት የአምላክ ሕዝቦች እውነተኛ ትንቢቶችን ተቀብለው የነበረ ቢሆንም የሐሰተኛ ነቢያትን የሚበክሉ ትምህርቶች መቋቋም አስፈልጓቸው ነበር። (ኤርምያስ 6:13, 14፤ 28:1-3, 15) ኤርምያስ “በኢየሩሳሌምም ነቢያት ላይ የሚያስደነግጥን ነገር አይቻለሁ፤ ያመነዝራሉ በሐሰትም ይሄዳሉ” ሲል ጽፏል።—ኤርምያስ 23:14
4. ሐሰተኛ አስተማሪዎች ጥፋት የሚገባቸው ለምንድን ነው?
4 ጴጥሮስ ሐሰተኛ አስተማሪዎች በክርስቲያን ጉባኤ ውስጥ ምን እንደሚያደርጉ ሲገልጽ “እነርሱም የዋጃቸውን ጌታ [ኢየሱስ ክርስቶስን] እንኳ ክደው የሚፈጥንን ጥፋት በራሳቸው ላይ እየሳቡ የሚያጠፋ ኑፋቄን አሹልከው ያገባሉ” ብሏል። (2 ጴጥሮስ 2:1፤ ይሁዳ 4) እንደምናውቀው እንዲህ ዓይነቱ የመጀመሪያው መቶ ዘመን ኑፋቄ የዛሬዋን ሕዝበ ክርስትና አፍርቷል። ጴጥሮስ ሐሰተኛ አስተማሪዎች በእርግጥም ጥፋት የሚገባቸው ለምን እንደሆነ ሲገልጽ “ብዙዎችም በመዳራታቸው ይከተሉአቸዋል በእነርሱም ጠንቅ የእውነት መንገድ ይሰደባል” ብሏል።—2 ጴጥሮስ 2:2
-
-
ከሐሰተኛ አስተማሪዎች ተጠንቀቁ!መጠበቂያ ግንብ—1997 | መስከረም 1
-
-
የሐሰት ትምህርቶችን ማስገባት
6. ሐሰተኛ አስተማሪዎችን የሚያነሳሳቸው ነገር ምንድን ነው? የሚፈልጉትን ነገር ለማግኘትስ የሚጣጣሩት እንዴት ነው?
6 የሐሰት አስተማሪዎች ብልሹ የሆነ ሐሳባቸውን ወደ ጉባኤው እንዴት እንደሚያስገቡ ማስተዋላችን ጥበብ ይሆናል። ጴጥሮስ በመጀመሪያ ትምህርታቸውን በረቀቀ መንገድ በስውር አሹልከው እንደሚያስገቡ ተናግሯል። አክሎም “የሚሸነግሉ ቃላት በመናገር ለራሳቸው ምኞት መጠቀሚያ ያደርጓችኋል” (NW) ብሏል። ዘ ጀሩሳሌም ባይብል “በመሠሪ ንግግር እናንተን ለማግባባት ከፍተኛ ጥረት ያደርጋሉ” በማለት የሐሰት አስተማሪዎችን የሚያነሳሳቸው የራስ ወዳድነት ምኞች እንደሆነ ጎላ አድርጎ ገልጿል። በተመሳሳይም የጄምስ ሞፋት ትርጉም ይህንኑ ጥቅስ “የሚያባብሉ ቃላት በመናገር ከመጠን በላይ ለሚጓጉለት ነገር መጠቀሚያ ያደርጓችኋል” ሲል ተርጉሞታል። (2 ጴጥሮስ 2:1, 3) የሐሰት አስተማሪዎች የሚናገሩት ነገር በመንፈሳዊ ንቁ ላልሆነ ሰው እውነት ሊመስል ይችላል፤ ይሁን እንጂ ንግግራቸው ሰዎች የስስት ፍላጎታቸውን እንዲያራምዱላቸው ‘ለማግባባት’ ሲባል በዘዴ የታቀደ ነው።
-