-
በተከፋፈለ ዓለም ውስጥ ክርስቲያናዊ የእንግዳ ተቀባይነት መንፈስ ማሳየትመጠበቂያ ግንብ—1996 | ጥቅምት 1
-
-
“እንግዲህ ከእውነት ጋር አብረን እንድንሠራ እኛ እንዲህ ያሉትን በእንግድነት ልንቀበል ይገባናል።”—3 ዮሐንስ 8
-
-
በተከፋፈለ ዓለም ውስጥ ክርስቲያናዊ የእንግዳ ተቀባይነት መንፈስ ማሳየትመጠበቂያ ግንብ—1996 | ጥቅምት 1
-
-
3. እውነተኛ ደስታና እርካታ ልናገኝ የምንችለው እንዴት ነው?
3 ሰዎች እንደ ይሖዋ ቢሆኑና ሌሎችን በደግነት፣ በልግስና፣ በእንግዳ ተቀባይነት መንፈስ ቢይዙ ሁኔታው ምንኛ የተለየ ይሆን ነበር! ይሖዋ እውነተኛ ደስታ የሚገኘው የየራሳችንን ፍላጎት ለማርካት ከመጣጣር እንዳልሆነ ግልጽ አድርጓል። የእውነተኛ ደስታ ቁልፉ የሚከተለው ነው። “ከሚቀበል ይልቅ የሚሰጥ ደስተኛ ነው።” (ሥራ 20:35) እውነተኛ ደስታና እርካታ ለማግኘት ከፈለግን እንቅፋት የሚሆኑብንን ከፋፋይ ድንበሮች ማሸነፍ ይኖርብናል። አብረውን ይሖዋን ለሚያገለግሉ ሰዎች እጃችንን መዘርጋት አለብን። “እንግዲህ ከእውነት ጋር አብረን እንድንሠራ እኛ እንዲህ ያሉትን በእንግድነት ልንቀበል ይገባናል” የሚለውን ምክር መከተል አለብን። (3 ዮሐንስ 8) ሁኔታችን በሚፈቅድልን መጠን ለሚገባቸው ሰዎች የእንግዳ ተቀባይነት መንፈስ ማሳየት በሁለት በኩል ጥቅም ያስገኛል። ሰጪውንም ተቀባዩንም ይጠቅማል። ታዲያ ‘በእንግድነት ልንቀበላቸው’ ከሚገቡ ሰዎች መካከል እነማን ይገኛሉ?
-