-
የአንባቢያን ጥያቄዎችመጠበቂያ ግንብ—2015 | ግንቦት 15
-
-
ይሁን እንጂ በራእይ 20:8 ላይ የተጠቀሰው ‘ጎግና ማጎግ’ ማንን ያመለክታል? በ1,000 ዓመቱ ፍጻሜ ላይ በሚኖረው የመጨረሻ ፈተና ወቅት በይሖዋ ላይ የሚያምፁት ሰዎች፣ በታላቁ መከራ መጨረሻ ላይ በአምላክ ሕዝቦች ላይ ጥቃት የሚሰነዝሩትና ‘የማጎጉ ጎግ’ የተባሉት ብሔራት የሚያሳዩት ዓይነት የነፍሰ ገዳይነት መንፈስ ያንጸባርቃሉ። የሁለቱም ቡድኖች የመጨረሻ ዕጣ ተመሳሳይ ይኸውም ዘላለማዊ ጥፋት ነው! (ራእይ 19:20, 21፤ 20:9) እንግዲያው በሺህ ዓመቱ ፍጻሜ ላይ የሚያምፁ ሁሉ ‘ጎግና ማጎግ’ ተብለው መጠራታቸው ተገቢ ይመስላል።
-